የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኮሪደር ልማትና ተያያዥ ግንባታዎች ከከተሞች የወደፊት ዕድገት ጋር የተሳሳሩ ናቸው - አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር)

Apr 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2017(ኢዜአ)፦ ኮሪደር ልማትና ተያያዥ ግንባታዎች ከከተሞች የወደፊት ዕድገት ጋር የተሳሳሩ ናቸው ሲሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የከተማ ልማት አስተባባሪና የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

ሃላፊው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ዛሬ ከክልላችን አመራሮች፣ ከሰሜን ሸዋ ዞን እና ከደብረብርሃን ከተማ አመራሮች ጋር በመሆን በደብረ ብርሃን ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራና ዘመናዊ የገበያ ማዕከል ግንባታ ፕሮጀክት የመስክ ምልከታ አድርገናል ብለዋል።


በደብረ ብርሃን ከተማ የኮሪደር ልማት መጀመሪያው ምዕራፍ ከጠባሴ መሳለሚያ እስከ በሬሳ ድልድይ ድረስ የ3 ኪሜ ግንባታ መሆኑን ገልጸው ይህም የመንገድ፣ የብስክሌት እና የእግረኛ መንገድን እንዲሁም መናፈሻዎችን ያካተተ ነው ብለዋል።

በተቀናጀ የአመራር ክትትል የመጀመሪያውን ምዕራፍ ቀሪ ስራዎችን በተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ሲሉም ገልጸዋል።


የኮሪደር ልማት ደብረ ብርሃን ከተማን ውብ ገጽታ በማላበስ ለኑሮ፣ ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ምቹነቷን የሚያሳድግ እንደሚሆን ገልጸው በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደርና በክልሉ መንግስት ትብብር እየተከናወነ ያለውን ዘመናዊ የገበያ ማዕከል ግንባታ ሂደት መመልከታቸውን ጠቁመዋል።

የገበያ ማዕከሉ በተጀመረበት የግንባታ ጥራት አግባብ በያዝነው ዓመት ቀሪ ወራት ሲጠናቀቅ አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የገበያ ዋጋን በዘላቂነት ለማረጋጋት ያስችላል ያሉት አሕመዲን መሐመድ(ዶ/ር) የማዕከሉ ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆንም ተገቢውን ድጋፍና ክትትል አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026