
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2017(ኢዜአ)፦ ኮሪደር ልማትና ተያያዥ ግንባታዎች ከከተሞች የወደፊት ዕድገት ጋር የተሳሳሩ ናቸው ሲሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የከተማ ልማት አስተባባሪና የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ሃላፊው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ዛሬ ከክልላችን አመራሮች፣ ከሰሜን ሸዋ ዞን እና ከደብረብርሃን ከተማ አመራሮች ጋር በመሆን በደብረ ብርሃን ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራና ዘመናዊ የገበያ ማዕከል ግንባታ ፕሮጀክት የመስክ ምልከታ አድርገናል ብለዋል።

በደብረ ብርሃን ከተማ የኮሪደር ልማት መጀመሪያው ምዕራፍ ከጠባሴ መሳለሚያ እስከ በሬሳ ድልድይ ድረስ የ3 ኪሜ ግንባታ መሆኑን ገልጸው ይህም የመንገድ፣ የብስክሌት እና የእግረኛ መንገድን እንዲሁም መናፈሻዎችን ያካተተ ነው ብለዋል።
በተቀናጀ የአመራር ክትትል የመጀመሪያውን ምዕራፍ ቀሪ ስራዎችን በተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ሲሉም ገልጸዋል።

የኮሪደር ልማት ደብረ ብርሃን ከተማን ውብ ገጽታ በማላበስ ለኑሮ፣ ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ምቹነቷን የሚያሳድግ እንደሚሆን ገልጸው በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደርና በክልሉ መንግስት ትብብር እየተከናወነ ያለውን ዘመናዊ የገበያ ማዕከል ግንባታ ሂደት መመልከታቸውን ጠቁመዋል።
የገበያ ማዕከሉ በተጀመረበት የግንባታ ጥራት አግባብ በያዝነው ዓመት ቀሪ ወራት ሲጠናቀቅ አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የገበያ ዋጋን በዘላቂነት ለማረጋጋት ያስችላል ያሉት አሕመዲን መሐመድ(ዶ/ር) የማዕከሉ ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆንም ተገቢውን ድጋፍና ክትትል አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026