የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በቬይትናም በሩዝ ምርት እና የእሴት ሰንሰለት ላይ በጋራ ሰፋፊ ስራዎችን መስራት የሚያስችሉ ስምምነቶች ተደርገዋል - ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር)

Apr 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 11/2017(ኢዜአ)፦ በቬይትናም ቆይታ በሩዝ ምርት እና የእሴት ሰንሰለት ላይ በጋራ ሰፋፊ ስራዎችን መስራት የሚያስችሉ ስምምነቶች መደረጋቸውን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለጹ።

ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቬይትናም ቆይታን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸውም ቬይትናም በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀጣይነት ያለው እድገት በማስመዝገብ መካከለኛ ገቢ ወዳላቸው ሀገራት የገባች መሆኗን አንስተዋል።

በተለይም የግብርና ልማቷን በማዘመን ትልቅ እድገት ማስመዝገቧን ተናግረዋል።

ባለፉት 20 እና 30 አመታት በግብርና ላይ በሰራችው ስራ አሁን ላይ በአለማችን ከፍተኛ የቡና አምራች እና ላኪ ሀገር መሆን መቻሏንም ገልጸዋል።

ኢትዮጵያም አንዷ ከፍተኛ የቡና አምራች ሀገር መሆኗን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ቬይትናም በሩዝ እና በአትክልት እንዲሁም ፍራፍሬ ትልቅ አቅም መፍጠሯን አንስተዋል።

ቡና ኤክስፖርት በማድረግ 4 ቢሊዮን ዶላር እንደምታገኝ ጠቅሰው፤ ከዚህም ብዙ ልምድ መውሰድ እንደሚቻል ተናግረዋል።

የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ አንጻርም በተለይ በሩዝ ላይ ትልቅ ስራ መስራቷን ለመመልከት መቻሉን ገልጸዋል።

በ7 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ ሩዝ በማልማት 24 ሚሊዮን ቶን ምርት እንደምታገኝ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያም ባለፉት ሁለት አመታት ወደ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ ሩዝ ማምረት መጀመሯን በመግለጽ።

በቬይትናም ቆይታም በስንዴ የተሰራውን ስራ በሩዝ ላይ መድገም የሚያስችል የተሞክሮ ልውውጥ ማድረግ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን አንስተዋል።

በሩዝ ምርት እና የእሴት ሰንሰለት ላይ በጋራ ሰፋፊ ስራዎችን መስራት የሚያስችሉ ስምምነቶች መደረጋቸውንም ጨምረው ገልጸዋል።

ከአትክልት እና ፍራፍሬ ስራዎች አንጻር የሚወሰደው ተሞክሮ ምርቶቹ ሳይበላሹ የሚጓጓዙበት ስርዓት መሆኑን ጠቅሰዋል።

በተጨማሪም ምርቶቹን ከመነሻቸው ጀምሮ የሚሰበሰቡበት መንገድም ልምድ የሚወሰድበት መሆኑን እና ይህም የድህረ ምርት ብክነት የቀነሱበትን መንገድ እንደሚያሳይም ተናግረዋል።

በታዳሽ ሀይል፣ በስማርት ሲቲ ግንባታ እንዲሁም ከተፈጥሮ ጋር የተላመደ የአኗኗር ዘዴያቸው አስደናቂ መሆኑን በመጥቀስ።

ቀጣይነት ያላቸውን ስራዎች ማከናወን ከተቻለ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ አደገ ኢኮኖሚ መሻገር እንደሚቻል ቬይትናም ማሳያ መሆኗንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025