
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 11/2017(ኢዜአ)፦ በመዲናዋ ለትንሳኤ በዓል የሚሆኑ የእርድ እንስሳት በበቂ መጠን መቅረባቸውን ኢዜአ ሲገበያዩ ያገኛቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለፁ።
ኢዜአ የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ የእርድ እንስሳት የግብይት ሁኔታን ተዘዋውሮ ተመልክቷል።
በዚህም የቁም እንስሳት ግብይት አቅርቦት በተሻለ ሁኔታ መኖሩንና መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ መታየቱን ሸማቾች ተናግረዋል።
በሾላ ገበያ ዶሮ እና እንቁላል ሲገበያዩ ያገኘናቸው ወይዘሮ ሙሉ እመቤት ታደሰ፤ ለበዓሉ በቂ የእንስሳት አቅርቦት እንዳለ አስተያየታቸው ሰጥተዋል።
በቂ አቅርቦት መኖሩ ሁሉም ባለው አቅም መርጦ በመግዛት በዓሉን እንዲያከብር ያስችለዋል ሲሉ ነው የጠቀሱት።
በአዲሱ ገበያ ሲገበያዩ ያገኘናቸው አቶ ይታገሱ በቀለ እና ስዩም ተፈራ በበኩላቸው፤ የዘንድሮው የትንሳኤ በዓል መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ ቢኖረውም ገበያው ላይ በቂ አቅርቦት በመኖሩ እንደአቅማቸው መግዛታቸውን ገልጸዋል።
የበግና ፍየል ገበያ ከሌሎቹ የበዓል ጊዜያት ጋር ሲነጻጸር መጠነኛ ጭማሪ ቢያሳይም ከአርሶ አደሮቹ በጥሩ ዋጋ መግዛት መቻላቸውን አቶ ዘሪሁን ወልዴ የተባሉ ሸማች ተናግረዋል።
አቶ ምሳዬ ተፈራ፣ አቶ አንዷለም እሸቴ እና አቶ ዘለቀ እጅጋየሁ በሰንጋ ገበያው በቂ አቅርቦት መኖሩን ነው የተናገሩት።
አስተያየት ሰጪዎቹ በአሉን ስናከብር ጧሪ የሌላቸውንና አቅመ ደካማ ወገኖችን በመጠየቅና ካለን በማካፈል ሊሆን ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
የበዓሉ አስተምህሮም ይህንኑ የሚያጎለብት መሆኑን አመልክተው፤ የበዓሉን እሴት አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልፀዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026