የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በመዲናዋ ለበዓል የሚሆኑ የእርድ እንስሳት በበቂ መጠን ቀርበዋል - ሸማቾች

Apr 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 11/2017(ኢዜአ)፦ በመዲናዋ ለትንሳኤ በዓል የሚሆኑ የእርድ እንስሳት በበቂ መጠን መቅረባቸውን ኢዜአ ሲገበያዩ ያገኛቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለፁ።

ኢዜአ የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ የእርድ እንስሳት የግብይት ሁኔታን ተዘዋውሮ ተመልክቷል።

በዚህም የቁም እንስሳት ግብይት አቅርቦት በተሻለ ሁኔታ መኖሩንና መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ መታየቱን ሸማቾች ተናግረዋል።

በሾላ ገበያ ዶሮ እና እንቁላል ሲገበያዩ ያገኘናቸው ወይዘሮ ሙሉ እመቤት ታደሰ፤ ለበዓሉ በቂ የእንስሳት አቅርቦት እንዳለ አስተያየታቸው ሰጥተዋል።

በቂ አቅርቦት መኖሩ ሁሉም ባለው አቅም መርጦ በመግዛት በዓሉን እንዲያከብር ያስችለዋል ሲሉ ነው የጠቀሱት።

በአዲሱ ገበያ ሲገበያዩ ያገኘናቸው አቶ ይታገሱ በቀለ እና ስዩም ተፈራ በበኩላቸው፤ የዘንድሮው የትንሳኤ በዓል መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ ቢኖረውም ገበያው ላይ በቂ አቅርቦት በመኖሩ እንደአቅማቸው መግዛታቸውን ገልጸዋል።

የበግና ፍየል ገበያ ከሌሎቹ የበዓል ጊዜያት ጋር ሲነጻጸር መጠነኛ ጭማሪ ቢያሳይም ከአርሶ አደሮቹ በጥሩ ዋጋ መግዛት መቻላቸውን አቶ ዘሪሁን ወልዴ የተባሉ ሸማች ተናግረዋል።

አቶ ምሳዬ ተፈራ፣ አቶ አንዷለም እሸቴ እና አቶ ዘለቀ እጅጋየሁ በሰንጋ ገበያው በቂ አቅርቦት መኖሩን ነው የተናገሩት።

አስተያየት ሰጪዎቹ በአሉን ስናከብር ጧሪ የሌላቸውንና አቅመ ደካማ ወገኖችን በመጠየቅና ካለን በማካፈል ሊሆን ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

የበዓሉ አስተምህሮም ይህንኑ የሚያጎለብት መሆኑን አመልክተው፤ የበዓሉን እሴት አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026