
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 13/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ይፋ ከተደረገ ጀምሮ የሚመረቱ ምርቶች ከአመት አመት አይነታቸው ጥራታቸው እና ተወዳዳሪነታቸው እያደገ መምጣቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን ሚያዚያ 29 ቀን 2014 ዓ.ም ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል።
ንቅናቄው በኢትየጵያ የተለያዩ ምርቶች እንዲመረቱ ከማስቻሉም በተጨማሪ ኢትዮጵያ ከውጭ የምታስገባቸውን ምርቶች በማስቀረት በኩል ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡
ሚኒስትር መላኩ አለበል ለኢዜአ እንደገለጹት የኢትየጵያ ታምርት ንቅናቄ ይፋ ከተደረገ ጀምሮ ባለፉት አመታት በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል፡፡
በዚህም ምርቶች ገበያ እንዲያገኙ እንዲሁም ትስስር አንዲፈጠርላቸው በማድረግ በኩል ትልቅ ሚና መጫወቱን ገልጸዋል፡፡

ባለፉት ሶስት ዓመታት የሚመረቱ ምርቶች ከአመት አመት አይነታቸው ጥራታቸውና ተወዳዳሪነታቸው እያደገ መምጣቱንም አስታውቀዋል፡፡
መንግስት ለማኑፋክቸሪንግ ትልቅ ትኩረት በመስጠት በዘርፉ የሚስተዋለውን የቅንጅት ችግር መቀረፉንም አስረድተዋል፡፡
ይህንን ተከትሎም አምራቾች ውጤታማ የማምረት ስራ ውስጥ መግባት መቻላቸውን አስታውቀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው፤ የማኑፋክቸሪንግ ካውንስል መቋቋሙና ወደ ስራ መግባቱን ለአብነት ጠቅሰዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026