
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 13/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ይፋ ከተደረገ ጀምሮ የሚመረቱ ምርቶች ከአመት አመት አይነታቸው ጥራታቸው እና ተወዳዳሪነታቸው እያደገ መምጣቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን ሚያዚያ 29 ቀን 2014 ዓ.ም ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል።
ንቅናቄው በኢትየጵያ የተለያዩ ምርቶች እንዲመረቱ ከማስቻሉም በተጨማሪ ኢትዮጵያ ከውጭ የምታስገባቸውን ምርቶች በማስቀረት በኩል ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡
ሚኒስትር መላኩ አለበል ለኢዜአ እንደገለጹት የኢትየጵያ ታምርት ንቅናቄ ይፋ ከተደረገ ጀምሮ ባለፉት አመታት በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል፡፡
በዚህም ምርቶች ገበያ እንዲያገኙ እንዲሁም ትስስር አንዲፈጠርላቸው በማድረግ በኩል ትልቅ ሚና መጫወቱን ገልጸዋል፡፡

ባለፉት ሶስት ዓመታት የሚመረቱ ምርቶች ከአመት አመት አይነታቸው ጥራታቸውና ተወዳዳሪነታቸው እያደገ መምጣቱንም አስታውቀዋል፡፡
መንግስት ለማኑፋክቸሪንግ ትልቅ ትኩረት በመስጠት በዘርፉ የሚስተዋለውን የቅንጅት ችግር መቀረፉንም አስረድተዋል፡፡
ይህንን ተከትሎም አምራቾች ውጤታማ የማምረት ስራ ውስጥ መግባት መቻላቸውን አስታውቀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው፤ የማኑፋክቸሪንግ ካውንስል መቋቋሙና ወደ ስራ መግባቱን ለአብነት ጠቅሰዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026