አንዳንዶቹ ከመደበኛ ግብርና ጎን ለጎን ያከናውኑታል ሌሎቹ ደግሞ ብቻውን የሙሉ ጊዜ ስራቸው መተዳደሪያቸው ያደርጉታል።
በደቡብ ምዕራብ ክልሏ ዳውሮ ዞን ሎማ ቦሳ ወረዳ በአንድ ቀበሌ ውስጥ ብቻ በ110 ዘመናዊ እና በ160 ባህላዊ የንብ ቀፎዎች እየተከናወነ ያለው የንብ ማነብ ስራ ውጤታማ እያደረጋቸው መሆኑን አርሶ አደሮቹ ይናገራሉ።
ኤላ ባቾ በተባለችው ቀበሌ ያሉት አርሶ አደሮቹ የማር ምርታቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመምጣቱም ተጠቃሚ አድርጓቸዋል።
የወረዳው ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ልማት ጽሕፈት ቤትም በዘርፉ ለተሰማሩ አርሶ አደሮች ሁለንተዊ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር እየሠራ መሆኑን ገልጿል።
በጽሕፈት ቤቱ እንስሳትና ዓሳ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መስፍን ገበየሁ እንደሚያስረዱት ቀደም ሲል ከአንድ ባህላዊ ቀፎ ከ4 እስከ 5 ኪሎ ግራም ማር ይገኝ ነበር።
አሁን በስፋት እየተሰራበት ባለው የሽግግር ቀፎም ከ20 እስከ 25 ኪሎ ግራም ማር እየተገኘ መሆኑን ያስረዳሉ።
ለዚህ ደግሞ ከቀፎ አዘገጃጀት ጀምሮ እስከ ማር ቆረጣ ድረስ በዘርፉ ከተሰማሩ አርሶ አደሮች ጋር በመሆን ሙያዊ ድጋፍ እያደረጉ እንደሚገኙም ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025