የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የንብ ማነብ ስራ የአብዛኛዎቹ አርሶ አደሮች ተግባር ነው

Apr 22, 2025

IDOPRESS

አንዳንዶቹ ከመደበኛ ግብርና ጎን ለጎን ያከናውኑታል ሌሎቹ ደግሞ ብቻውን የሙሉ ጊዜ ስራቸው መተዳደሪያቸው ያደርጉታል።

በደቡብ ምዕራብ ክልሏ ዳውሮ ዞን ሎማ ቦሳ ወረዳ በአንድ ቀበሌ ውስጥ ብቻ በ110 ዘመናዊ እና በ160 ባህላዊ የንብ ቀፎዎች እየተከናወነ ያለው የንብ ማነብ ስራ ውጤታማ እያደረጋቸው መሆኑን አርሶ አደሮቹ ይናገራሉ።

ኤላ ባቾ በተባለችው ቀበሌ ያሉት አርሶ አደሮቹ የማር ምርታቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመምጣቱም ተጠቃሚ አድርጓቸዋል።


የወረዳው ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ልማት ጽሕፈት ቤትም በዘርፉ ለተሰማሩ አርሶ አደሮች ሁለንተዊ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር እየሠራ መሆኑን ገልጿል።

በጽሕፈት ቤቱ እንስሳትና ዓሳ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መስፍን ገበየሁ እንደሚያስረዱት ቀደም ሲል ከአንድ ባህላዊ ቀፎ ከ4 እስከ 5 ኪሎ ግራም ማር ይገኝ ነበር።

አሁን በስፋት እየተሰራበት ባለው የሽግግር ቀፎም ከ20 እስከ 25 ኪሎ ግራም ማር እየተገኘ መሆኑን ያስረዳሉ።

ለዚህ ደግሞ ከቀፎ አዘገጃጀት ጀምሮ እስከ ማር ቆረጣ ድረስ በዘርፉ ከተሰማሩ አርሶ አደሮች ጋር በመሆን ሙያዊ ድጋፍ እያደረጉ እንደሚገኙም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025