
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 14/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮ-ሳውዲ አረቢያ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፎረም በሪያድ መካሄድ ጀምሯል።
በፎረሙ ከሁለቱም ሀገራት የተውጣጡ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የቢዝነስ መሪዎችና የንግዱ ማህበረሰብ ተሳትፈዋል።

በተያያዘም የኢትዮ-ሳዑዲ አረቢያ የጋራ ንግድ ምክር ቤት ስብሰባ በሪያድ ተካሂዷል።
ስብሰባውን በኢትዮጵያ ወገን የንግድ ምክር ቤቱ ሊቀመንበር ሃሰን አብዱላሂ(ዶ/ር) እና በሳዑዲ ወገን የጋራ ምክር ቤቱ ሊቀመንበር አብድላህ አላጃሚ በጋራ መርተውታል።
በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን ታሪካዊ ትብብር በኢኮኖሚው ዘርፍ ማጠናከር እንደሚገባ ተገልጿል።
መድረኩ በሀገራቱ መካከል አዲስ የኢኮኖሚ ትብብር እና የስትራቴጂክ አጋርነት ምዕራፍ እንደሚፈጥር ተነስቷል።
በስብሰባው በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ በተለይም በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ፣ በግብርና፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም እና በኮንስትራክሽን ዘርፎች አብሮ ለመስራት መስማማታቸውን በሪያድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026