የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኢትዮ-ሳውዲ አረቢያ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፎረም በሪያድ መካሄድ ጀመረ

Apr 23, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 14/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮ-ሳውዲ አረቢያ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፎረም በሪያድ መካሄድ ጀምሯል።

በፎረሙ ከሁለቱም ሀገራት የተውጣጡ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የቢዝነስ መሪዎችና የንግዱ ማህበረሰብ ተሳትፈዋል።


በተያያዘም የኢትዮ-ሳዑዲ አረቢያ የጋራ ንግድ ምክር ቤት ስብሰባ በሪያድ ተካሂዷል።

ስብሰባውን በኢትዮጵያ ወገን የንግድ ምክር ቤቱ ሊቀመንበር ሃሰን አብዱላሂ(ዶ/ር) እና በሳዑዲ ወገን የጋራ ምክር ቤቱ ሊቀመንበር አብድላህ አላጃሚ በጋራ መርተውታል።

በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን ታሪካዊ ትብብር በኢኮኖሚው ዘርፍ ማጠናከር እንደሚገባ ተገልጿል።

መድረኩ በሀገራቱ መካከል አዲስ የኢኮኖሚ ትብብር እና የስትራቴጂክ አጋርነት ምዕራፍ እንደሚፈጥር ተነስቷል።

በስብሰባው በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ በተለይም በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ፣ በግብርና፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም እና በኮንስትራክሽን ዘርፎች አብሮ ለመስራት መስማማታቸውን በሪያድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026