
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 14/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮ-ሳውዲ አረቢያ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፎረም በሪያድ መካሄድ ጀምሯል።
በፎረሙ ከሁለቱም ሀገራት የተውጣጡ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የቢዝነስ መሪዎችና የንግዱ ማህበረሰብ ተሳትፈዋል።

በተያያዘም የኢትዮ-ሳዑዲ አረቢያ የጋራ ንግድ ምክር ቤት ስብሰባ በሪያድ ተካሂዷል።
ስብሰባውን በኢትዮጵያ ወገን የንግድ ምክር ቤቱ ሊቀመንበር ሃሰን አብዱላሂ(ዶ/ር) እና በሳዑዲ ወገን የጋራ ምክር ቤቱ ሊቀመንበር አብድላህ አላጃሚ በጋራ መርተውታል።
በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን ታሪካዊ ትብብር በኢኮኖሚው ዘርፍ ማጠናከር እንደሚገባ ተገልጿል።
መድረኩ በሀገራቱ መካከል አዲስ የኢኮኖሚ ትብብር እና የስትራቴጂክ አጋርነት ምዕራፍ እንደሚፈጥር ተነስቷል።
በስብሰባው በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ በተለይም በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ፣ በግብርና፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም እና በኮንስትራክሽን ዘርፎች አብሮ ለመስራት መስማማታቸውን በሪያድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026