የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኢትዮ-ሳውዲ አረቢያ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፎረም በሪያድ መካሄድ ጀመረ

Apr 23, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 14/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮ-ሳውዲ አረቢያ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፎረም በሪያድ መካሄድ ጀምሯል።

በፎረሙ ከሁለቱም ሀገራት የተውጣጡ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የቢዝነስ መሪዎችና የንግዱ ማህበረሰብ ተሳትፈዋል።


በተያያዘም የኢትዮ-ሳዑዲ አረቢያ የጋራ ንግድ ምክር ቤት ስብሰባ በሪያድ ተካሂዷል።

ስብሰባውን በኢትዮጵያ ወገን የንግድ ምክር ቤቱ ሊቀመንበር ሃሰን አብዱላሂ(ዶ/ር) እና በሳዑዲ ወገን የጋራ ምክር ቤቱ ሊቀመንበር አብድላህ አላጃሚ በጋራ መርተውታል።

በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን ታሪካዊ ትብብር በኢኮኖሚው ዘርፍ ማጠናከር እንደሚገባ ተገልጿል።

መድረኩ በሀገራቱ መካከል አዲስ የኢኮኖሚ ትብብር እና የስትራቴጂክ አጋርነት ምዕራፍ እንደሚፈጥር ተነስቷል።

በስብሰባው በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ በተለይም በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ፣ በግብርና፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም እና በኮንስትራክሽን ዘርፎች አብሮ ለመስራት መስማማታቸውን በሪያድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026