
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 16/2017(ኢዜአ)፦ የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ5ሺህ 430 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል ማመንጨቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ።
የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከዕቅዱ በላይ ኃይል ማምረቱን የጣቢያው የኦፕሬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ደጀኔ ጉታ ገልጸዋል፡፡

ከማመንጫ ጣቢያው በ2017 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት 4ሺህ 725 ነጥብ 56 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ለማመንጨት ታቅዶ 5ሺህ 436 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማምረት መቻሉንም ተናግረዋል፡፡
ይህም ከዕቅዱ የ710 ነጥብ 94 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የ15 ነጥብ 04 በመቶ እንዲሁም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ189 ነጥብ 65 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የ3 ነጥብ 61 በመቶ ብልጫ እንዳለውም አስታውቀዋል፡፡

አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ማምረት የሚያስችሉ የፍተሻና የክትትል ሥራዎች በየጊዜው መከናወናቸው፣ የኦፕሬሽን ሥራው የተቋሙ ሥራ አመራር ባፀደቀው የኦፕሬሽን ሥራዎች የአሰራር ስርዓት ማኑዋል መሰረት መከናወኑ እና የኃይል መቋረጥ አመላካቾችና ችግሮች(alarms and faults) ሲስተዋሉ ወዲያውኑ እንዲወገዱ መደረጋቸው ለውጤቱ ምክንያቶች ናቸው ብለዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ መጨረሻ 6ሺህ 141 ነጥብ 49 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን አስታውሰው ባለፉት ዘጠኝ ወራትም ከአጠቃላይ ዕቅዱ የ88 ነጥብ 52 በመቶ አፈጻፀም ማስመዝገብ ተችሏል ነው ያሉት፡፡
ይህም በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት አመላካች እንደሆነም አቶ ደጀኔ ጉታ ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026