የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ሙስናን ለመከላከል በተደረገው ጥረት ከ85 ሚሊዮን በላይ ብር የህዝብ ሃብት ማዳን ተችላል

Apr 27, 2025

IDOPRESS

ቦንጋ፣ሚያዚያ 18/2017 (ኢዜአ):- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሙስናን ለመከላከል በተደረገው ጥረት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ85 ሚሊዮን ብር በላይ የመንግሥትና የህዝብ ሃብት ከምዝበራ ማዳን መቻሉ ተገለጸ።


የክልሉ ስነ-ምግባርና ፀረሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሉሰው ዘውዴ ለኢዜአ እንዳሉት፥ ኮሚሽኑ ሙስናን የመከላከል ተግባር ላይ የህብረተሰቡን ድርሻ ለማሳደግ ግንዛቤን የማስፋት ስራ ተጠናክሮ እየተሰራ ነው።


የሙስና ወንጀልን ቀድሞ በመከላከልና ተፈፅሞ ሲገኝም ማስረጃ በመተንተን ለፍትህ አካላት የማቅረብ ስራ በትኩረት መሰራቱን ገልጸዋል።


በዚህም በበጀት ዓመቱ ባለፉት 9 ወራት ኮሚሽኑ በተለያዩ ዘዴዎች ከተቀበላቸው 475 የሙስና ወንጀል ጥቆማዎች ውስጥ 399 ጉዳዮችን በማጣራት ውሳኔዎች እንደተላለፈባቸው እና ቀሪዎቹ በሂደት ላይ እንዳሉ ተናግረዋል።


በአስቸኳይ ሙስና መከላከል ስራ ከ39 ሚሊዮን 822 ሺህ ብር በላይ ማዳን የተቻለ ሲሆን በአሰራር ጥሰት ባክኖ የነበረ ከ45 ሚሊዮን 267 ሺህ ብር በላይ በኦዲት ግኝት እንዲመለስ መደረጉን ኮሚሽነር ሙሉሰው ጠቁመዋል።


ከገንዘብ በተጨማሪ ከ15 ሺህ 183 ካሬ በላይ የከተማ መሬት እና 353 ሄክታር የገጠር መሬት እንዲሁም ሌሎች በርካታ ንብረቶችን ማዳንና ማስመለስ ተችሏል ብለዋል።


ሙስናን መከላከል የሚያስችሉ ችግር ፈቺ ጥናቶችን ማካሄድ፣ የሀብት ምዝገባና ማሳወቅ እንዲሁም ትክክለኛነቱን የማጣራት ስራም ኮሚሽኑ ትኩረት የሰጠው ሌላኛው ተግባር መሆኑንም ተናግረዋል።


በተሰራው ስራም ባለፉት ዘጠኝ ወራት የ3 ሺህ 54 አዳዲስ የመንግስት ሰራተኞችን ሀብት የማስመዝገበ እና የምስክር ወረቀት የመስጠት ስራ መሠራቱንም ኮሚሽነር ሙሉሰው አንስተዋል።


ከሚሽኑ ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል በሚያደርገው ጥረት ህብረተሰቡ የሚያደርገውን ጥቆማዎችን እንዲያጠናክርም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026