
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 18/2017 (ኢዜአ)፦የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ወገኖች ላይ ጫና እንዳያሳድር የታቀዱ የድጋፍ መርሐ ግብሮች መከናወናቸውን የብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ።
በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራው የገቢ አሰባሰብ መሻሻሉ፣የልማት ፋይናንስ ዕድገት መመዝገቡ፣የወጪ አስተዳደርና የዕዳ ጫና ማቃለል ላይ ውጤታማ ለውጦች መመዝገባቸውም ተገልጿል።
የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ለሁለት ቀናት ያካሔደው ጉባኤ ተጠናቋል።
የጉባኤውን መጠናቀቅ ተከትሎ በወጣው መግለጫ፤ የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊ፣ማኅበራዊና ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች በዝርዝር ተዳሰዋል፡፡
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎች ላይ ጫና እንዳይፈጠር፣ለደመወዝ፣ ለዘይት፣ለሴፍቲኔት፣ለመድሃኒት፣ ለነዳጅ እና ለማዳበሪያ ከፍተኛ የድጎማ በጀት መመደቡ ተመላክቷል።
በዚህም ለማዳበሪያ 62 ቢሊዮን ብር፣ ለሴፍቲኔት 41 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር፣ ለነዳጅ 60 ቢልዮን ብር፣ ለመድኃኒት 3 ነጥብ 5 ቢልዮን ብር፣ ለምግብ ዘይት 6 ነጥብ 1 ቢልዮን ብር፣ እንዲሁም ለደመወዝ 38 ነጥብ 4 ቢልዮን ብር ድጎማ መደረጉን በመግለጫው በዝርዝር ቀርቧል።
ባለፉት 9 ወራት ብቻ 344 ሺህ 790 የውጭ ሀገር ሕጋዊ የሥራ ዕድሎች እና ከ3 ሚሊዮን በላይ የሀገር ውስጥ የሥራ ዕድሎች መፈጠራቸውም ነው የተገለጸው፡፡
የልማት ተቋማትን በአዲስ አስተሳሰብና በአዲስ መንገድ መልሶ ለማደራጀትና ለመምራት መቻሉን ያመለከተው መግለጫው፥ እያስገኘ ያለው ውጤትም ለሌሎች አርአያ መሆኑን የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው መገምገሙ በመግለጫው ተጠቅሷል።
የውጭ ምንዛሬ ክምችት እንዲሁም የባንኮች ተቀማጭ ገንዘብ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ 9 ወራት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ዕድገት ማሳየቱም በመግለጫው ተመልክቷል፡፡
የተሟላ ማክሮ የኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ የልማት ፋይናንስ ግኝትና ፍሰትን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደጉን ፤ የውጭ ምንዛሬ አስተዳደር ማሻሻያ መደረጉም ትልቅ ለውጥ ማምጣቱን መግለጫው ጠቅሷል።
ማሻሻያው አካታች የኢኮኖሚ ግንባታንና የኑሮ ጫናን ማቅለልን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እየተተገበረ መሆኑም ተብራርቷል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026