
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 18/2017 (ኢዜአ)፡- በአዲስ አበባ ከተማ ነገ ለሚደረገው የኢትዮጵያ ታምርት የ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ለተሽከርካሪዎችና ለእግረኞች ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የከተማዋ ፖሊስ ይፋ አድርጓል፡፡
የውድድሩ መነሻ ቦታ መስቀል አደባባይ ሲሆን ለገሃር መብራት፣ ቡናና ሻይ ሜክሲኮ አደባባይ፣ አፍሪካ ህብረት ሳር ቤት (ፑሽኪን አደባባይ)፣ ቄራ አዲሱ መሿለኪያ ድልድይ፣ ጎተራ ማሳለጫ፣ አጎና ሲኒማ፣ ግሎባል ሆቴል፣ መስከረም ማዞሪያ፣ ጥላሁን አደባባይ፣ ሳንጆሴፍ መብራት አድርጎ መስቀል አደባባይ ያበቃል።
በዚህም መሠረት :-
* ከቅዱስ ዑራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ባምቢስ መቅረዝ ሆስፒታል መስቀለኛ ላይ )
* ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ)
* ከብሔራዊ ቤተመንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ (ብሔራዊ ቤተመንግሥት ላይ)
* ከሀራምቤ መብራት ወደ ሳንጆሴፍ መብራት
* ከብሔራዊ ቲያትር ወደ ለገሀር መብራት
* ከሠንጋ ተራ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
* ከአረቄ ፋብሪካ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
* ከልደታ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
* ከልደታ ፀበል ወደ አፍሪካ ህብረት መብራት
* ከካርል አደባባይ ወደ ሳር ቤት አደባባይ
* ከቫቲካን ወደ ሳርቤት አደባባይ
* ከቄራ አልማዝዬ ሜዳ ወደ ቄራ መብራት
* ከጎፋ ገብርኤል አቅጣጫ ወደ ጎፋ መስቀለኛ በስር
* ከዮሴፍ ወደ ጎተራ ማሳለጫ
* ከመስቀል ፍላዎር ወደ አጎና መስቀለኛ
* ከጋዜቦ አደባባይ ወደ በቅሎ ቤት ድልድይ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ይዘጋሉ።
በተጠቀሱት መስመሮችም ከዛሬ ምሽት 12 ሠዓት ጀምሮ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026