አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 18/2017 (ኢዜአ)፡- በአዲስ አበባ ከተማ ነገ ለሚደረገው የኢትዮጵያ ታምርት የ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ለተሽከርካሪዎችና ለእግረኞች ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የከተማዋ ፖሊስ ይፋ አድርጓል፡፡
የውድድሩ መነሻ ቦታ መስቀል አደባባይ ሲሆን ለገሃር መብራት፣ ቡናና ሻይ ሜክሲኮ አደባባይ፣ አፍሪካ ህብረት ሳር ቤት (ፑሽኪን አደባባይ)፣ ቄራ አዲሱ መሿለኪያ ድልድይ፣ ጎተራ ማሳለጫ፣ አጎና ሲኒማ፣ ግሎባል ሆቴል፣ መስከረም ማዞሪያ፣ ጥላሁን አደባባይ፣ ሳንጆሴፍ መብራት አድርጎ መስቀል አደባባይ ያበቃል።
በዚህም መሠረት :-
* ከቅዱስ ዑራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ባምቢስ መቅረዝ ሆስፒታል መስቀለኛ ላይ )
* ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ)
* ከብሔራዊ ቤተመንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ (ብሔራዊ ቤተመንግሥት ላይ)
* ከሀራምቤ መብራት ወደ ሳንጆሴፍ መብራት
* ከብሔራዊ ቲያትር ወደ ለገሀር መብራት
* ከሠንጋ ተራ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
* ከአረቄ ፋብሪካ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
* ከልደታ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
* ከልደታ ፀበል ወደ አፍሪካ ህብረት መብራት
* ከካርል አደባባይ ወደ ሳር ቤት አደባባይ
* ከቫቲካን ወደ ሳርቤት አደባባይ
* ከቄራ አልማዝዬ ሜዳ ወደ ቄራ መብራት
* ከጎፋ ገብርኤል አቅጣጫ ወደ ጎፋ መስቀለኛ በስር
* ከዮሴፍ ወደ ጎተራ ማሳለጫ
* ከመስቀል ፍላዎር ወደ አጎና መስቀለኛ
* ከጋዜቦ አደባባይ ወደ በቅሎ ቤት ድልድይ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ይዘጋሉ።
በተጠቀሱት መስመሮችም ከዛሬ ምሽት 12 ሠዓት ጀምሮ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025