የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ልማት ሽግግርን የሚያሳልጥ ምህዳር ተፈጥሯል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር

May 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 22/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ልማት ሽግግርን የሚያሳልጥ ምህዳር መፈጠሩን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ(ዶ/ር) ገለጹ።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ቁልፍ የልማት ዘርፎች ላይ የቴክኖሎጂ ልማትና ሽግግርን የማሳለጥ ዓላማን ያነገበ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ በማካሄድ ላይ ይገኛል።

ኢትዮጵያ የስታርት አፕ እና የቴክኖሎጂ ፈጠራ ማዕከል እየሆነች ነው - ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር)

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ(ዶ/ር) እንዳሉት የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ልማትን ለማሳለጥ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።


በዚህም በኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ልማትና ግንባታ ሽግግርን የሚያሳልጥ ምህዳር መፈጠሩን አስታውቀዋል።

ባለፉት ሰባት ዓመታትም የክህሎትና የፈጠራ ልማትን ለማስፋት የሰው ሃብት ልማት፣ የፖሊሲ ዝግጅትና የአሰራር ሥርዓት በመፍጠር ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል።

የዲጂታል ቴክኖሎጂ ልማትን ለማስፋትም ከተቋማት ጋር በመተባበር በመንግስትና የግል አጋርነት ጭምር ቀጣይነት ያላቸው ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል።


በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዜጎችን የቴክኖሎጂ ዕውቀትና ክህሎት ለማበልጸግ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የ5 ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠና ወሳኝ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

ዜጎችም በ5 ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠና ላይ በንቃት በመሳተፍ የቴክኖሎጂ ዕውቀትና ክህሎታቸውን ማበልጸግ የሚችሉበትን ዕድል መጠቀም እንዳለባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመድረኩ በባዮ እና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ፣ በስፔስ ሳይንስና ጂኦ-ስፓሻል፣ በቴክኖሎጂ ልማትና ሽግግር ከሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ፖሊሲ መስኮች ላይ የቴክኖሎጂ ልማትና ሽግግር ጉዳዮች ላይ የመነሻ ጽሁፎች ቀርበው ምክክር እንደሚደረግባቸው ተጠቅሷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025