
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 27/2017(ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ከተማዋን ውብ ገፅታ ያላበሱና የህብረተሰቡን የአኗኗር ዘይቤ የቀየሩ ናቸው ሲሉ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች ገለፁ።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት እየተሰሩ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራዎች አዲስ አበባን ዘላቂነት ባለው አግባብ ለዜጎች ምቹ እና ውብ እያደረጓት ይገኛል።

ልማቱ የከተማዋን ገፅታ ከመሰረቱ ከመቀየር ባሻገር ለነዋሪዎቿ ምቹና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንድትሆን እያንደረደራትም ይገኛል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን አስመልክቶ ከነዋሪዎች ጋር ቆይታ አድርጓል፡፡
አቶ ኤርሚያሰ ተገኔ በመዲናዋ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ከተማዋን ውብ ገፅታ ያላበሱና የህብረተሰቡን የአኗኗር ዘይቤ የቀየሩ ናቸው ፣ ለሰው ልጆች ምቹ እና አስፈላጊ በሆነ መልኩ መገንባቱን ተናግረዋል።
የተገነቡት የመናፈሻ ቦታዎች፣ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶች የራስን ጤና ከመጠበቅ ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳላቸው ነው የተናገሩት ።

የፈረንሳይ ለጋሲዮን ነዋሪ የሆነችው ሃይማኖት አብርሃም በበኩሏ በከተማዋ እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎች አበረታች ናቸው ብላለች።
በሁሉም የከተማዋ አካባቢዎች የተሰሩ የልማት ስራዎች እንዳይበላሹ ነዋሪዎች በሃላፊነት መጠቀም እና መንከባከብ እንዳለበት ተናግራለች።
አቶ ሀይለማርያም ኪዳኔ ለ40 አመታት በካዛንችስ አካባቢ መኖራቸውን ተናግረው ከዚህ ቀደም የነበረውን የአካባቢውን ገጽታ ሙሉ በሙሉ የቀየረና ውብ ገጽታ ያላበሰ ግንባታ መመልከታቸውን ተናግረዋል።

በካዛንቺስ የተከናወኑት የኮሪደር ልማት ስራዎች እጅግ የሚደነቁና አስደናቂ ውበት የተላበሱ መሆናቸውን ነው የተናገሩት።

እየተሰራ ያሉ ስራዎች ትውልድን ማዕከል ያደረጉ በመሆናቸው የሚበረታታ ነው ያሉት የመዲናዋ ነዋሪ የሆኑት አቶ ዘላለም ጀምበሩ ናቸው።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026