
ጅማ፣ሚያዚያ 27/2017(ኢዜአ)፦የንብ ማነብ ስራን በዘመናዊ መንገድ በማከናወን የማር ምርትን ለማሳደግ የተጀመረው ስራ ይጠናከራል ሲሉ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለጹ።
በጅማ ከተማ የማር ኤግዚቢሽን የተከፈተ ሲሆን በኤግዚቢሽኑ ላይ የፌዴራል፣የክልልና የዞን የስራ ሀላፊዎች እንዲሁም ማር አምራቾችና ነጋዴዎች ተሳትፈዋል።
ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት፥ ኢትዮጵያ ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ ያላት ሀገር ናት።
ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ ባህላዊውን የንብ ማነብ ስራ ወደ ዘመናዊ መቀየሩ በትኩረት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
በተለይም በኦሮሚያ ክልል ለማር አምራቾች ዘመናዊ ቀፎ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ተደራሽ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
የማር ምርትን ለማዘመን ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ እንደ ሀገር 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዘመናዊ ቀፎ መሰራጨቱን የገለጹት ሚኒስትሩ ከዚህም 250 ሺህ ቶን የማር ምርት ተገኝቷል ብለዋል።
የንብ ማነብ ስራን የበለጠ በማዘመን ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ የተጀመሩ ስራዎች እንደሚጠናከሩ አስታውቀዋል።
የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ጉቱ ገመቹ በበኩላቸው፥ በክልሉ ከአራት አመት በፊት የተጀመረው የማር ምርት ኢኒሼቲቭ ትልቅ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ገልጸዋል።
እየተካሄደ በሚገኘው የማር ምርት ኢኒሼቲቭ ባህላዊ የንብ ቀፎን በዘመናዊ በመተካት የማር ምርት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።
በክልሉ የማር ምርትን ለማሳደግ በተደረገ እንቅስቃሴ በዚህ አመት 140 ሺህ ቶን ማር መገኘቱን ተናግረዋል።
የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር፣ በዞኑ በግብርና ልማት ኢኒሼቲቮች የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል::
በዞኑ በሁሉም ወረዳዎች እየተተገበሩ ያሉ ኢኒቬቲቮች ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸው፥ በማር ምርትም የተሻለ እመርታ መታየቱን ጠቅሰዋል።
በማር ምርት ኢግዚቢሽኑ የተሳተፉ አምራቾች በበኩላቸው፥ መንግስት በተመጣጣኝ ዋጋ ባቀረበላቸው የዘመናዊ ቀፎ ምርታቸው መጨመሩን ገልጸዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026