የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የንብ ማነብ ስራን በዘመናዊ መንገድ በማከናወን የማር ምርትን ለማሳደግ የተጀመረው ስራ ይጠናከራል-ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)

May 6, 2025

IDOPRESS

ጅማ፣ሚያዚያ 27/2017(ኢዜአ)፦የንብ ማነብ ስራን በዘመናዊ መንገድ በማከናወን የማር ምርትን ለማሳደግ የተጀመረው ስራ ይጠናከራል ሲሉ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለጹ።


በጅማ ከተማ የማር ኤግዚቢሽን የተከፈተ ሲሆን በኤግዚቢሽኑ ላይ የፌዴራል፣የክልልና የዞን የስራ ሀላፊዎች እንዲሁም ማር አምራቾችና ነጋዴዎች ተሳትፈዋል።


ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት፥ ኢትዮጵያ ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ ያላት ሀገር ናት።


ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ ባህላዊውን የንብ ማነብ ስራ ወደ ዘመናዊ መቀየሩ በትኩረት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።


በተለይም በኦሮሚያ ክልል ለማር አምራቾች ዘመናዊ ቀፎ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ተደራሽ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።


የማር ምርትን ለማዘመን ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ እንደ ሀገር 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዘመናዊ ቀፎ መሰራጨቱን የገለጹት ሚኒስትሩ ከዚህም 250 ሺህ ቶን የማር ምርት ተገኝቷል ብለዋል።


የንብ ማነብ ስራን የበለጠ በማዘመን ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ የተጀመሩ ስራዎች እንደሚጠናከሩ አስታውቀዋል።


የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ጉቱ ገመቹ በበኩላቸው፥ በክልሉ ከአራት አመት በፊት የተጀመረው የማር ምርት ኢኒሼቲቭ ትልቅ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ገልጸዋል።


እየተካሄደ በሚገኘው የማር ምርት ኢኒሼቲቭ ባህላዊ የንብ ቀፎን በዘመናዊ በመተካት የማር ምርት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።


በክልሉ የማር ምርትን ለማሳደግ በተደረገ እንቅስቃሴ በዚህ አመት 140 ሺህ ቶን ማር መገኘቱን ተናግረዋል።


የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር፣ በዞኑ በግብርና ልማት ኢኒሼቲቮች የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል::


በዞኑ በሁሉም ወረዳዎች እየተተገበሩ ያሉ ኢኒቬቲቮች ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸው፥ በማር ምርትም የተሻለ እመርታ መታየቱን ጠቅሰዋል።


በማር ምርት ኢግዚቢሽኑ የተሳተፉ አምራቾች በበኩላቸው፥ መንግስት በተመጣጣኝ ዋጋ ባቀረበላቸው የዘመናዊ ቀፎ ምርታቸው መጨመሩን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026