የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ትውልዱ ከቀድሞ አባቶች በመማር ድህነትን በመዋጋት የዘመኑ አርበኝነቱን ማረጋገጥ ይገባዋል-የክህሎት ውድድር ተሳታፊዎች

May 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 27/2017 (ኢዜአ)፡-ትውልዱ ከቀድሞ አባቶቹ ድል አድራጊነትን በመማር ድህነትን በመዋጋት የዘመኑ አርበኛነቱን ማረጋገጥ እንዳለበት አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአራተኛው አገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ተሳታፊዎች ገለፁ።


ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አራተኛውን አገር አቀፍ የክህሎት ውድድር "ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ሃሳብ በይፋ አስጀምረዋል።


በክህሎት ውድድሩ ስራቸውን ካቀረቡት መካከል ወርቅአፈራሁ ሻፊ እንዳለው፥ በውድድሩ በውጭ ምንዛሬ ወደ አገር ውስጥ ይገባ የነበረውን የሰብል መውቂያ ማሽን በፈጠራ በመስራት ማቅረባቸውን ተናግሯል።


ማሽኑ በሰዓት እስከ 15 ኩንታል እህል የሚወቃና ተረፈ ምርቱም ለከብቶች መኖ እንዲውል ማድረግ የሚያስችል እንደሆነም ገልጿል።


በቆጮ አዘገጃጀት ላይ ፈጠራቸውን ይዘው የመጡ መምህር ተስፋዬ ታደሰ በበኩላቸው፥ከዚህ ቀደም እናቶች በባህላዊ መንገድ ቆጮን ሲያዘጋጁ ልፋትና እንግልት እንደሚገጥማቸው ያነሳሉ።


ይዘው የቀረቡት ቴክኖሎጂ የእናቶችን ችግር የሚያቃልል፣ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድግና የቆጮ ጥራትን የሚያስጠብቅ መሆኑንም ተናግረዋል።


የፈጠራ ባለቤት ደምስ ኪዳኔ በበኩሉ፥ የሰሩት ማሽን የሽመናና የልብስ ምርትን ለማዘመን የሚያስችል ነው።


ማሽኑ በሞተሩ ውጭ ሙሉ በሙሉ በአገር ውስጥ ግብዓት የተሰራ መሆኑን የገለፀ ሲሆን ከሽመና በተጨማሪ የተለያዩ ልብሶችንና ጨርቆችን ማምረት የሚያስችል ነው።


የአርበኞች ቀን የቀድሞ አባቶቻችን ወራሪ ጠላትን ድል በመንሳት ነፃነትን የተቀዳጁበት መሆኑን አውስተው፤የአሁኑ ትውልድ ከዚህ ትምህርት በመውሰድ ድህነትን መዋጋት አለበት ብለዋል።


የዘመኑ አርበኝነት ድህነት ላይ መዝመትን የሚጠይቅ በመሆኑ ትውልዱ የአገር ምርት በመጠቀም፣ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥና በምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት ድህነትን መዋጋት እንደሚገባው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025