አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 27/2017 (ኢዜአ)፡-ትውልዱ ከቀድሞ አባቶቹ ድል አድራጊነትን በመማር ድህነትን በመዋጋት የዘመኑ አርበኛነቱን ማረጋገጥ እንዳለበት አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአራተኛው አገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ተሳታፊዎች ገለፁ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አራተኛውን አገር አቀፍ የክህሎት ውድድር "ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ሃሳብ በይፋ አስጀምረዋል።
በክህሎት ውድድሩ ስራቸውን ካቀረቡት መካከል ወርቅአፈራሁ ሻፊ እንዳለው፥ በውድድሩ በውጭ ምንዛሬ ወደ አገር ውስጥ ይገባ የነበረውን የሰብል መውቂያ ማሽን በፈጠራ በመስራት ማቅረባቸውን ተናግሯል።
ማሽኑ በሰዓት እስከ 15 ኩንታል እህል የሚወቃና ተረፈ ምርቱም ለከብቶች መኖ እንዲውል ማድረግ የሚያስችል እንደሆነም ገልጿል።
በቆጮ አዘገጃጀት ላይ ፈጠራቸውን ይዘው የመጡ መምህር ተስፋዬ ታደሰ በበኩላቸው፥ከዚህ ቀደም እናቶች በባህላዊ መንገድ ቆጮን ሲያዘጋጁ ልፋትና እንግልት እንደሚገጥማቸው ያነሳሉ።
ይዘው የቀረቡት ቴክኖሎጂ የእናቶችን ችግር የሚያቃልል፣ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድግና የቆጮ ጥራትን የሚያስጠብቅ መሆኑንም ተናግረዋል።
የፈጠራ ባለቤት ደምስ ኪዳኔ በበኩሉ፥ የሰሩት ማሽን የሽመናና የልብስ ምርትን ለማዘመን የሚያስችል ነው።
ማሽኑ በሞተሩ ውጭ ሙሉ በሙሉ በአገር ውስጥ ግብዓት የተሰራ መሆኑን የገለፀ ሲሆን ከሽመና በተጨማሪ የተለያዩ ልብሶችንና ጨርቆችን ማምረት የሚያስችል ነው።
የአርበኞች ቀን የቀድሞ አባቶቻችን ወራሪ ጠላትን ድል በመንሳት ነፃነትን የተቀዳጁበት መሆኑን አውስተው፤የአሁኑ ትውልድ ከዚህ ትምህርት በመውሰድ ድህነትን መዋጋት አለበት ብለዋል።
የዘመኑ አርበኝነት ድህነት ላይ መዝመትን የሚጠይቅ በመሆኑ ትውልዱ የአገር ምርት በመጠቀም፣ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥና በምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት ድህነትን መዋጋት እንደሚገባው ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025