
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 27/2017 (ኢዜአ)፡-ትውልዱ ከቀድሞ አባቶቹ ድል አድራጊነትን በመማር ድህነትን በመዋጋት የዘመኑ አርበኛነቱን ማረጋገጥ እንዳለበት አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአራተኛው አገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ተሳታፊዎች ገለፁ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አራተኛውን አገር አቀፍ የክህሎት ውድድር "ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ሃሳብ በይፋ አስጀምረዋል።
በክህሎት ውድድሩ ስራቸውን ካቀረቡት መካከል ወርቅአፈራሁ ሻፊ እንዳለው፥ በውድድሩ በውጭ ምንዛሬ ወደ አገር ውስጥ ይገባ የነበረውን የሰብል መውቂያ ማሽን በፈጠራ በመስራት ማቅረባቸውን ተናግሯል።
ማሽኑ በሰዓት እስከ 15 ኩንታል እህል የሚወቃና ተረፈ ምርቱም ለከብቶች መኖ እንዲውል ማድረግ የሚያስችል እንደሆነም ገልጿል።
በቆጮ አዘገጃጀት ላይ ፈጠራቸውን ይዘው የመጡ መምህር ተስፋዬ ታደሰ በበኩላቸው፥ከዚህ ቀደም እናቶች በባህላዊ መንገድ ቆጮን ሲያዘጋጁ ልፋትና እንግልት እንደሚገጥማቸው ያነሳሉ።
ይዘው የቀረቡት ቴክኖሎጂ የእናቶችን ችግር የሚያቃልል፣ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድግና የቆጮ ጥራትን የሚያስጠብቅ መሆኑንም ተናግረዋል።
የፈጠራ ባለቤት ደምስ ኪዳኔ በበኩሉ፥ የሰሩት ማሽን የሽመናና የልብስ ምርትን ለማዘመን የሚያስችል ነው።
ማሽኑ በሞተሩ ውጭ ሙሉ በሙሉ በአገር ውስጥ ግብዓት የተሰራ መሆኑን የገለፀ ሲሆን ከሽመና በተጨማሪ የተለያዩ ልብሶችንና ጨርቆችን ማምረት የሚያስችል ነው።
የአርበኞች ቀን የቀድሞ አባቶቻችን ወራሪ ጠላትን ድል በመንሳት ነፃነትን የተቀዳጁበት መሆኑን አውስተው፤የአሁኑ ትውልድ ከዚህ ትምህርት በመውሰድ ድህነትን መዋጋት አለበት ብለዋል።
የዘመኑ አርበኝነት ድህነት ላይ መዝመትን የሚጠይቅ በመሆኑ ትውልዱ የአገር ምርት በመጠቀም፣ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥና በምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት ድህነትን መዋጋት እንደሚገባው ተናግረዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026