
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 28/2017(ኢዜአ)፦ኢንዱስትሪዎች በገበያ ተወዳዳሪ ለመሆን ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂ ታግዘው ጥራቱን የጠበቀ ምርት ማምረት እንዳለባቸው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሦስተኛውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በይፋ መርቀው መክፈታቸው ይታወሳል።
በዚህም የኤክስፖው አካል የሆኑ ፓናል ውይይቶች በተለያዩ ባለድርሻ አካላት በመካሄድ ላይ የሚገኙ ሲሆን በመድረኩ በአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ላይ ያተኮረ ውይይ ተካሂዷል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ኢንዱስትሪዎች በምርትና አገልግሎት አሰጣጥ ተወዳዳሪ ለመሆን ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂ ሊታገዙ ይገባል፡፡
ከለውጡ በኋላ የተጀመረው የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂና የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ፕሮግራም የዜጎችን የቴክኖሎጂ ክህሎት ከማዳበር ባለፈ ለግሉ ዘርፍ ምቹ አውድ የፈጠረ ነው ብለዋል።
ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ዘመኑ የደረሰበት የ4ጂ እና 5ጂ ኔትወርክ ተደራሽ በማድረግና የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ በማድረግ ረገድም ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቅሰዋል፡፡
በዚህም ግልጽነትና አስተማማኝነት ያለው አገልግሎት የሚሰጡ ኦንላይን ፕላትፎርሞች መፈጠራቸው በዘርፉ ለተገኙ ለውጦች ማሳያ መሆናቸውን አመላክተዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት በመተካት የውጭ ምንዛሪ ወጪን ለመቀነስ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ጠቁመዋል፡፡
የፈጠራ ውጤቶች ለማስፋትና የፈጠራ ሃሳቦችን በማዳበር ወደ ተግባር ለመቀየር በኢኖቬሽን ማዕከላት እና በዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ሊንኬጅ አማካኝነት የጥናትና ምርምር ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ትላልቅ ኢንዱስትሪዎች በፈጠራ ውጤታቸውና በቴክኖሎጂ አጠቃቀማቸው ለአነስተኛና መለስተኛ ኢንዱስትሪዎች ምርጥ ተሞክሯቸውን እንዲያካፍሉ በጥናትና ምርምር የመደገፍ ስራ በመሰራት ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል ፡፡
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026