
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 28/2017(ኢዜአ)፦ኢንዱስትሪዎች በገበያ ተወዳዳሪ ለመሆን ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂ ታግዘው ጥራቱን የጠበቀ ምርት ማምረት እንዳለባቸው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሦስተኛውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በይፋ መርቀው መክፈታቸው ይታወሳል።
በዚህም የኤክስፖው አካል የሆኑ ፓናል ውይይቶች በተለያዩ ባለድርሻ አካላት በመካሄድ ላይ የሚገኙ ሲሆን በመድረኩ በአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ላይ ያተኮረ ውይይ ተካሂዷል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ኢንዱስትሪዎች በምርትና አገልግሎት አሰጣጥ ተወዳዳሪ ለመሆን ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂ ሊታገዙ ይገባል፡፡
ከለውጡ በኋላ የተጀመረው የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂና የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ፕሮግራም የዜጎችን የቴክኖሎጂ ክህሎት ከማዳበር ባለፈ ለግሉ ዘርፍ ምቹ አውድ የፈጠረ ነው ብለዋል።
ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ዘመኑ የደረሰበት የ4ጂ እና 5ጂ ኔትወርክ ተደራሽ በማድረግና የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ በማድረግ ረገድም ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቅሰዋል፡፡
በዚህም ግልጽነትና አስተማማኝነት ያለው አገልግሎት የሚሰጡ ኦንላይን ፕላትፎርሞች መፈጠራቸው በዘርፉ ለተገኙ ለውጦች ማሳያ መሆናቸውን አመላክተዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት በመተካት የውጭ ምንዛሪ ወጪን ለመቀነስ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ጠቁመዋል፡፡
የፈጠራ ውጤቶች ለማስፋትና የፈጠራ ሃሳቦችን በማዳበር ወደ ተግባር ለመቀየር በኢኖቬሽን ማዕከላት እና በዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ሊንኬጅ አማካኝነት የጥናትና ምርምር ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ትላልቅ ኢንዱስትሪዎች በፈጠራ ውጤታቸውና በቴክኖሎጂ አጠቃቀማቸው ለአነስተኛና መለስተኛ ኢንዱስትሪዎች ምርጥ ተሞክሯቸውን እንዲያካፍሉ በጥናትና ምርምር የመደገፍ ስራ በመሰራት ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል ፡፡
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026