የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ ኢትዮጵያ አባል ለመሆን ያቀረበችውን ጥያቄ ተቀበለ

May 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፡- የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ ኢትዮጵያ ባንኩን ለመቀላቀል ያቀረበችውን ጥያቄ መቀበሉን አስታወቀ።

ባንኩ ኢትዮጵያ አባል ለመሆን የሚያስችላትን የድርድር ሂደት እንድትጀምር ጋብዟል።

ይህ ለኢትዮጵያ በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ትልቅ ስኬት የሚባል መሆኑን በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው በመጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ከባንኩ ፕሬዝዳንት ዲልማ ሩሴፍ ጋር መወያየታቸው የሚታወስ ነው።

በውይይቱም ኢትዮጵያ ለባለብዙ ወገን የፋይናንስ ትብብር እና ከባንኩ ጋር በተለያዩ መስኮች በትብብር ለመስራት ቁርጠኛ እንደሆነች መግለጿን ኤምባሲው በመረጃው አስታውሷል።

ኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ (በቀድሞ አጠራሩ የብሪክስ ልማት ባንክ) በብሪክስ አባል ሀገራት እ.አ.አ በ2014 ተቋቁሞ ከአንድ ዓመት በኋላ በ2015 ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025