አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፡- የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ ኢትዮጵያ ባንኩን ለመቀላቀል ያቀረበችውን ጥያቄ መቀበሉን አስታወቀ።
ባንኩ ኢትዮጵያ አባል ለመሆን የሚያስችላትን የድርድር ሂደት እንድትጀምር ጋብዟል።
ይህ ለኢትዮጵያ በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ትልቅ ስኬት የሚባል መሆኑን በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው በመጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ከባንኩ ፕሬዝዳንት ዲልማ ሩሴፍ ጋር መወያየታቸው የሚታወስ ነው።
በውይይቱም ኢትዮጵያ ለባለብዙ ወገን የፋይናንስ ትብብር እና ከባንኩ ጋር በተለያዩ መስኮች በትብብር ለመስራት ቁርጠኛ እንደሆነች መግለጿን ኤምባሲው በመረጃው አስታውሷል።
ኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ (በቀድሞ አጠራሩ የብሪክስ ልማት ባንክ) በብሪክስ አባል ሀገራት እ.አ.አ በ2014 ተቋቁሞ ከአንድ ዓመት በኋላ በ2015 ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025