
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ኢትዮጵያ የማምረት አቅም እና ብሩህ ተስፋ እንዳላት የሚያሳይ መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገለጹ።
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል የሚከናወነውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2017 ጎብኝተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሚያዚያ 25 እስከ 29 ቀን 2017 ዓ.ም የሚቆየውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2017 በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል።
በኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከ288 በላይ አምራቾች እየተሳተፉበት ነው፡፡

ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ከጉብኝቱ በኋላ በሰጡት ማብራሪያ፤ የኢትዮጵያ ፍላጎት ምርታማነትን በመጨመር ጥቅል ሀገራዊ እድገትን ማሻሻል መሆኑን ገልጸዋል።
በኤክስፖው የቀረቡት ከቆዳ የተሰሩ የተለያዩ ምርቶች በዓለም አቀፍ የጥራት መመዘኛ መስፈርት ደረጃቸውን ያሟሉ መሆናቸውን ተመልክቻለሁ ብለዋል።
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶችን ማምረት ከማስቻሉም በላይ የኢትዮጵያን የገበያ መዳረሻ የሚያሰፋ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

የአምራች ኢንዱስትሪውን የማምረት አቅም በማሳደግ የሥራ እድል የሚፈጥርና ነገ የተሻለ ለማምረት መሰረት የሚጥል መሆኑን ገልጸዋል።
ማምረት የአንድ ሀገር እድገት መሰረት መሆኑን የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤ በማምረት ላይ የተሰማሩ ሀገራት ከፍ ያለ እድገት ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
በኤክስፖው የታየው መነቃቃት የማምረት አቅማችንን ያሳድጋል ያሉትፕሬዝዳንቱ፣የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ኢትዮጵያ የማምረት አቅም እና ብሩህ ተስፋ እንዳላት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026