
አርባ ምንጭ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ከተሞች የትብብር መድረክ ከተሞች ልምዳቸውን በመለዋወጥ ለእድገታቸው የተሻለ ግብዓት እያገኙበት መሆኑን ገለጹ።
በኢትዮጵያ ከተሞች የትብብር መድረክ አዘጋጅነት የአራት ክልሎች ከተሞች ከንቲባዎች የተሳተፉበት ስልጠናዊ አውደ ጥናት በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ ላይም የኢትዮጵያ ከተሞች የትብብር መድረክ ዋና ዳይሬክተር አቶ አንዷለም ጤናው እንደገለጹት የከተሞችን የእርስ በርስ ትስስር በማጠናከር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማትን ለማረጋገጥ ጥረት እየተደረገ ነው።
በተለይም ከተሞች የውስጥ ገቢያቸውን በማሳደግ የህዘቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ሊመልሱ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
የትብብር መድረኩ 108 አባል ከተሞችን በአባልነት መያዙን ጠቅሰው በመድረኩም ከተሞች ልምድ እየተለዋወጡ ለእድገታቸው የተሻለ ግብዓት እያገኙበት መሆኑን አስረድተዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ወይዘሮ የምስራች ገመዴ በበኩላቸው የትብብር መድረኩ እያደገ የመጣውን የነዋሪዎች የአገልግሎትና የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የተሻለ ልምድ የሚቀሰምበት መሆኑን ተናግረዋል።
በክልሉ ከተሞችን በማዘመን ለነዋሪዎች ምቹና ጽዱ ለማድረግ እንዲሁም የቱሪስት መዳረሻነታቸውን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
የአርባ ምንጭ ከተማ ከንቲባ መስፍን መንዛ(ዶ/ር) በከተማው የኮሪደር ልማትና የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች እንዲሁም የመሠረተ ልማት ግንባታዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።
በተጨማሪም የከተማዋን የገቢ አቅም ለማሳደግ የሚያግዙ የተለያዩ ፕሮጀክቶችም እየተተገበሩ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።
ለሁለት ቀናት በተዘጋጀው መድረክ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ በሲዳማ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች የሚገኙ የ22 ከተማ ከንቲባዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026