የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም ለሚደረገው ጥረት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እገዛ ተጠናክሮ ይቀጥላል - ሚኒስቴሩ

May 12, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ ግንቦት 1/2017(ኢዜአ)፦ የአከባቢ ብክለትን ለመከላከልና ተፅዕኖውን ለመቋቋም ለሚደረገው ጥረት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እገዛ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል ትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ።

5ኛው ዓለም አቀፍ የጥናትና ምርምር ሲምፖዝየም በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው።

በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈፃሚ ኤባ ሚጀና(ዶ/ር)፤ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ስራዎች የማህበረሰቡን ችግሮች የሚፈቱ ሊሆኑ እንደሚገባ ገልጸዋል።

በመሆኑም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም ለሚደረገው ጥረት እገዛቸው ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል።


የምርምር ሲምፖዚየሙ ዓላማም የፕላስቲክና የወረቀት ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ እንዲሁም የግብርና እና የኢንዱስትሪ ተረፈ ምርቶችን አያያዝ፤ መልሰው መጠቀምና ወደ ሃብት መቀየርን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን አንስተዋል።


የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዘዳንት ተሾመ አብዶ(ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው በሳይንስና ቴክኖሎጂ ብቁና ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ከማፍራት ባለፈ ችግር ፈቺ የምርምር ስራዎች ላይ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

በተለይ በህዋ ሳይንስ፤ ፋርማሲዩቲካል፤ ድሮን ቴክኖሎጂና አውቶሞቲቭን ጨምሮ አምስት የልህቀት ማዕከላትን ወደ ሙሉ የምርምር ስራ ለማስገባት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ዩኒቨርሲቲው 20 ክልላዊና የፌዴራል ሜጋ ፕሮጄክቶችን የማማከር ስራ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው በአይሲቲ መሰረተ ልማት ዝርጋታና በሶፍትዌሮች ልማት ላይ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በምርምር ሲምፖዝየሙ ከሀገር ውስጥ ዩኒቨርሲቲዎች፤ ከደቡብ ኮሪያ፤ ከህንድና ከአውስትራሊያ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና የምርምር ተቋማት ተሳታፊ ሆነዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025