የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም ለሚደረገው ጥረት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እገዛ ተጠናክሮ ይቀጥላል - ሚኒስቴሩ

May 12, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ ግንቦት 1/2017(ኢዜአ)፦ የአከባቢ ብክለትን ለመከላከልና ተፅዕኖውን ለመቋቋም ለሚደረገው ጥረት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እገዛ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል ትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ።

5ኛው ዓለም አቀፍ የጥናትና ምርምር ሲምፖዝየም በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው።

በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈፃሚ ኤባ ሚጀና(ዶ/ር)፤ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ስራዎች የማህበረሰቡን ችግሮች የሚፈቱ ሊሆኑ እንደሚገባ ገልጸዋል።

በመሆኑም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም ለሚደረገው ጥረት እገዛቸው ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል።


የምርምር ሲምፖዚየሙ ዓላማም የፕላስቲክና የወረቀት ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ እንዲሁም የግብርና እና የኢንዱስትሪ ተረፈ ምርቶችን አያያዝ፤ መልሰው መጠቀምና ወደ ሃብት መቀየርን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን አንስተዋል።


የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዘዳንት ተሾመ አብዶ(ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው በሳይንስና ቴክኖሎጂ ብቁና ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ከማፍራት ባለፈ ችግር ፈቺ የምርምር ስራዎች ላይ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

በተለይ በህዋ ሳይንስ፤ ፋርማሲዩቲካል፤ ድሮን ቴክኖሎጂና አውቶሞቲቭን ጨምሮ አምስት የልህቀት ማዕከላትን ወደ ሙሉ የምርምር ስራ ለማስገባት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ዩኒቨርሲቲው 20 ክልላዊና የፌዴራል ሜጋ ፕሮጄክቶችን የማማከር ስራ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው በአይሲቲ መሰረተ ልማት ዝርጋታና በሶፍትዌሮች ልማት ላይ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በምርምር ሲምፖዝየሙ ከሀገር ውስጥ ዩኒቨርሲቲዎች፤ ከደቡብ ኮሪያ፤ ከህንድና ከአውስትራሊያ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና የምርምር ተቋማት ተሳታፊ ሆነዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026