
ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 1/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሚካሄደው የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ሁሉም የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ጥሪ አቀረቡ።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና ሌሎችም የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተወካዮች በተገኙበት ተጀምሯል።
በዚሁ መርሃ ግብር እስከ ሰኔ 2017 ዓ.ም በክልሉ 900 ሺህ ዜጎችን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ለማድረግ እቅድ መያዙም ታውቋል።
በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ ንግግር ያደረጉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፤ የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚ ጉዞ ለማረጋገጥ በመንግስት ከፍተኛ ጥረትና ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ለዚህም የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮጀክት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፥ ዲጂታሉን ዓለም በመቀላቀል ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት ሁሉም የፋይዳ ምዝገባ ማድረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።
በክልሉ ለሚካሄደው የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ሁሉም የዕድሉ ተጠቃሚ ሊሆን ይገባል ሲሉም ተናግረዋል።
በክልሉ ከዛሬ ጀምሮ ለሚከናወነው የፋይዳ ምዝገባ አስከ ሰኔ 2017 ዓ.ም 900 ሺህ ዜጎችን የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት የማድረግ እቅድ መኖሩን ጠቅሰው፥ እድሉን ተጠቀሙበት በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
የክልሉ መንግስት ለስራው መሳካት አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል የሚያደርግ መሆኑንም አረጋግጠዋል።
በክልሉ ከዛሬ ጀምሮ እየተካሄደ ባለው ምዝገባም በርካቶች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለመሆን እየተመዘገቡ መሆኑም ገልፀዋል።
በክልሉ በዘመቻ የተጀመረው የምዝገባ ስርዓት እስከ ክልሉ ገጠር አካባቢዎች ድረስም ተደራሽ እንደሚሆን ተገልጿል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026