ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 1/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሚካሄደው የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ሁሉም የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ጥሪ አቀረቡ።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና ሌሎችም የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተወካዮች በተገኙበት ተጀምሯል።
በዚሁ መርሃ ግብር እስከ ሰኔ 2017 ዓ.ም በክልሉ 900 ሺህ ዜጎችን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ለማድረግ እቅድ መያዙም ታውቋል።
በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ ንግግር ያደረጉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፤ የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚ ጉዞ ለማረጋገጥ በመንግስት ከፍተኛ ጥረትና ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ለዚህም የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮጀክት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፥ ዲጂታሉን ዓለም በመቀላቀል ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት ሁሉም የፋይዳ ምዝገባ ማድረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።
በክልሉ ለሚካሄደው የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ሁሉም የዕድሉ ተጠቃሚ ሊሆን ይገባል ሲሉም ተናግረዋል።
በክልሉ ከዛሬ ጀምሮ ለሚከናወነው የፋይዳ ምዝገባ አስከ ሰኔ 2017 ዓ.ም 900 ሺህ ዜጎችን የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት የማድረግ እቅድ መኖሩን ጠቅሰው፥ እድሉን ተጠቀሙበት በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
የክልሉ መንግስት ለስራው መሳካት አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል የሚያደርግ መሆኑንም አረጋግጠዋል።
በክልሉ ከዛሬ ጀምሮ እየተካሄደ ባለው ምዝገባም በርካቶች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለመሆን እየተመዘገቡ መሆኑም ገልፀዋል።
በክልሉ በዘመቻ የተጀመረው የምዝገባ ስርዓት እስከ ክልሉ ገጠር አካባቢዎች ድረስም ተደራሽ እንደሚሆን ተገልጿል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025