
ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 1/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሚካሄደው የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ሁሉም የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ጥሪ አቀረቡ።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና ሌሎችም የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተወካዮች በተገኙበት ተጀምሯል።
በዚሁ መርሃ ግብር እስከ ሰኔ 2017 ዓ.ም በክልሉ 900 ሺህ ዜጎችን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ለማድረግ እቅድ መያዙም ታውቋል።
በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ ንግግር ያደረጉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፤ የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚ ጉዞ ለማረጋገጥ በመንግስት ከፍተኛ ጥረትና ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ለዚህም የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮጀክት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፥ ዲጂታሉን ዓለም በመቀላቀል ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት ሁሉም የፋይዳ ምዝገባ ማድረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።
በክልሉ ለሚካሄደው የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ሁሉም የዕድሉ ተጠቃሚ ሊሆን ይገባል ሲሉም ተናግረዋል።
በክልሉ ከዛሬ ጀምሮ ለሚከናወነው የፋይዳ ምዝገባ አስከ ሰኔ 2017 ዓ.ም 900 ሺህ ዜጎችን የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት የማድረግ እቅድ መኖሩን ጠቅሰው፥ እድሉን ተጠቀሙበት በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
የክልሉ መንግስት ለስራው መሳካት አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል የሚያደርግ መሆኑንም አረጋግጠዋል።
በክልሉ ከዛሬ ጀምሮ እየተካሄደ ባለው ምዝገባም በርካቶች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለመሆን እየተመዘገቡ መሆኑም ገልፀዋል።
በክልሉ በዘመቻ የተጀመረው የምዝገባ ስርዓት እስከ ክልሉ ገጠር አካባቢዎች ድረስም ተደራሽ እንደሚሆን ተገልጿል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026