የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ ለሚካሄደው የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ሁሉም የዕድሉ ተጠቃሚ ሊሆን ይገባል- ርእሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

May 12, 2025

IDOPRESS

ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 1/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሚካሄደው የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ሁሉም የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ጥሪ አቀረቡ።


በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና ሌሎችም የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተወካዮች በተገኙበት ተጀምሯል።


በዚሁ መርሃ ግብር እስከ ሰኔ 2017 ዓ.ም በክልሉ 900 ሺህ ዜጎችን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ለማድረግ እቅድ መያዙም ታውቋል።


በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ ንግግር ያደረጉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፤ የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚ ጉዞ ለማረጋገጥ በመንግስት ከፍተኛ ጥረትና ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።


ለዚህም የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮጀክት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፥ ዲጂታሉን ዓለም በመቀላቀል ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት ሁሉም የፋይዳ ምዝገባ ማድረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።


በክልሉ ለሚካሄደው የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ሁሉም የዕድሉ ተጠቃሚ ሊሆን ይገባል ሲሉም ተናግረዋል።


በክልሉ ከዛሬ ጀምሮ ለሚከናወነው የፋይዳ ምዝገባ አስከ ሰኔ 2017 ዓ.ም 900 ሺህ ዜጎችን የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት የማድረግ እቅድ መኖሩን ጠቅሰው፥ እድሉን ተጠቀሙበት በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።


የክልሉ መንግስት ለስራው መሳካት አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል የሚያደርግ መሆኑንም አረጋግጠዋል።


በክልሉ ከዛሬ ጀምሮ እየተካሄደ ባለው ምዝገባም በርካቶች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለመሆን እየተመዘገቡ መሆኑም ገልፀዋል።


በክልሉ በዘመቻ የተጀመረው የምዝገባ ስርዓት እስከ ክልሉ ገጠር አካባቢዎች ድረስም ተደራሽ እንደሚሆን ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026