
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2017(ኢዜአ)፦በከተማዋ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች የአመራር ቁርጠኝነትና የመተባበር ውጤትን በተግባር ያሳዩ ናቸው ሲሉ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ።
አዲስ አበባ የዓለም የዲፕሎማሲ መዲና፣ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ፣ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ እንቅስቃሴ ማዕከል መሆኗን ተከትሎ ከተማዋን የሚመጥን የልማት ስራ በሰፊው በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
በከተማዋ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት በአገር አቀፍ ደረጃ ጥሩ መነቃቃት የፈጠረ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ ነው።

የኮሪደር ልማት ዜጎችን ወደ ዘመናዊ አኗኗር በማሸጋገር የከተሞች ተወዳዳሪነት እንዲጨምር ከማድረጉ ባሻገር እንደ አገር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳውም የጎላ ነው።
ኢዜአ በመዲናዋ በተለያዩ የኮሪደር ልማት ስፍራዎች አግኝቶ ያነጋገራቸው አስተያየት ሰጪዎች እንደገለጹት የኮሪደር ልማቱ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትን አጎናጽፏታል።
በኮሪደር ልማት የተከናወኑ መሰረተ ልማቶች ሳቢና ምቹ ከመሆናቸው ባሻገር አማራጭ የመዝናኛ ስፍራዎችን መፍጠራቸውን ነው የተናገሩት።

የከተማዋን ውበት የሚጨምሩ የመንገድ መሰረተ ልማቶች፣ የመዝናኛ ሥፍራዎችና ማረፊያዎች መኖራቸው ከተማዋ እያደገችና ተወዳዳሪ እየሆነች መምጣቷን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።
ለ18 አመታት ኑሯቸውን በኖርዌይ ያደረጉት ወይዘሮ አምሳለ መላከብርሃን እንደገለጹት በአዲስ አበባ በየወቅቱ የሚታዩት አዳዲስ ልማቶች ግርምትን የሚፈጥሩ ናቸው።
በተለይም የኮሪደር ልማቱና የዚሁ አካል የሆኑ የልማት ስራዎች መንግስት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረትና ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ በመሆኑ በእጅጉ መደሰታቸውነ ገልጸው ስራው እንደ አገር የሚያኮራ ተግባር ነው ብለዋል።

ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ኤልያስ ኦኩማ በበኩላቸው የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ዘመናዊነትን እያላበሳት መሆኑን መስክረዋል።
ለዜጎች ምቹ ስፍራንና ሁኔታን ለመፍጠር መንግስት ያሳየው ቁርጠኝነት በእጅጉ የሚደነቅና የሚያስመሰግን መሆኑንም ገልጸዋል።
በመሆኑም ጎብኚዎች አዲሲቷን ኢትዮጰያ መጥተው እንዲጎበኙ ጥሪ አቅርበዋል።
አስተያየት ሰጪዎቹ አክለውም የኮሪደር ልማቱ አማራጭ የመዝናኛ ስፍራዎችን የፈጠረ በመሆኑ ሰዎች የእረፍት ጊዜያቸውንና የተለያዩ ኹነቶቻቸውን በቀላሉ ለማሳለፍ ምቹ እድል እንደተፈጠረላቸው አክለዋል።

ወይዘሮ መዲና ዑመር የተባሉ አስተያየት ሰጪ እንደገለጹት የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር በዘለለ አዳዲስ የመዝናኛና የህጻናት መጫወቻ ስፍራዎች እንዲገነቡ እድል ፈጥሯል።
በሁሉም መስክ የሚከናወኑ የልማት ስራዎች ካላቸው ፋይዳ በዘለለ ቀጣዩን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉና የበለጸገች አገር የማውረስ ተልእኮን የሚያሳኩ ናቸው ያሉት ደግሞ አቶ ስንታየሁ ደንድር ናቸው።

ቀደም ሲል ህጻናትን ለማጫወትና ለማዝናናት በቂ ስፍራዎች እንዳልነበሩ ጠቁመው የኮሪደር ልማቱ አካል የሆኑ የመዝናኛ ስፍራዎች በቀላል ዋጋና በቅርቡ መኖራቸው እንዳስደሰታቸው ጠቁመዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026