
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ 2025 የቢዝነስ ፎረም በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
በፎረሙ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ፣ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ፣ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ እና ሌሎች ሚኒስትሮች ተገኝተዋል።

የቢዝነስ ፎረሙ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እና በአጋር የልማት ድርጅቶች የተዘጋጀ ነው።
በተጨማሪም በፎረሙ የዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ ታዋቂ ኩባንያዎች፣ የንግዱ ማህበረሰብ መሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ አማካሪዎች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ታድመዋል።
ለሶስተኛ ጊዜ የሚካሄደው በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ የቢዝነስ ፎረም ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ተቀዳሚ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ከማድረግ ባለፈ ዘላቂና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት የመፍጠር አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል።
አዳዲስ ኢንቨስትመንትን መሳብ፣ መንግስት ለዘርፉ የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት ማሳየት እና አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፖሊሲ ማሻሻያዎችን ማሳወቅ ከፎረሙ ዓላማዎች መካከል ይገኙበታል።
ዛሬና ነገ በሚካሄደው ፎረም በርካታ የዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ ታዋቂ ኩባንያዎች ይሳተፋሉ።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026