
ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፦የወላይታ ሶዶ ግብርና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በመሳተፍ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ የውስጥ ገቢውን እያሳደገ መሆኑን አስታወቀ።
የኮሌጁ ዲን አሉላ ታፈሰ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፥ ኮሌጁ ከመማር ማስተማር ሥራ በተጨማሪ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በእንስሳትና በዶሮ ልማት ውጤታማ ሥራ እያከናወነ ይገኛል።
በመርሃ ግብሩ የሚያመርታቸውን ምርቶች ለማህበረሰቡ ከማቅረብ ባለፈ በዘርፉ ላይ የህብረተሰቡን ግንዛቤ የማሳደግ ተግባር እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
የሥጋ ዶሮዎችን፣ እንቁላልና የወተት ምርቶችን ጨምሮ የተለያዩ አትክልቶችን በማምረት ለአካባቢው ነዋሪዎች በቅናሽ ዋጋ በማቅረብ ገበያ የማረጋጋት ሥራ እያከናወነ መሆኑንም አመልክተዋል።
ኮሌጁ የወተት ምርት ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እንደሚያቀርብ ገልጸው፣ በዚህም ለአካባቢው ማህበረሰብ የሚሰጠውን አገልግሎት ከማጠናከር ባለፈ የኮሌጁን የውስጥ ገቢ እያሳደገ ነው ብለዋል።
ኮሌጁ በሚያከናውናቸው የሌማት ትሩፋት ሥራዎች ከ100 በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች ቋሚ እና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፍጠሩንም አሉላ (ዶ/ር) ተናግረዋል።
በእንስሳት እርባታ ዘርፍ ሰፋፊ ሥራዎች መጀመራቸውን የገለጹት ደግሞ በኮሌጁ የእንስሳት እርባታ ባለሙያ አቶ በረከት በቀለ፥ ህብረተሰቡ በኮሌጁ የሌማት ትሩፋት ሥራ በተለያየ መንገድ ተጠቃሚ እየሆነ ነው።
ኮሌጁ ምርቶችን በዝቅተኛ ዋጋ ከማቅረብ ባለፈ በዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ላይ የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ ለሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ስኬታማነት የበኩሉን እየተወጣ መሆኑንም አመልክተዋል።
ኮሌጁ ወተትና እንቁላልን ጨምሮ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን በቅናሽ ዋጋ በማቅረብ ገበያውን እያረጋጋ መሆኑን የገለጹት ደግሞ ወይዘሮ ማለዳወርቅ ሉቃስ የተባሉ የአካባቢው ነዋሪ ናቸው።
ህብረተሰቡ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በዘላቂነት ተጠቃሚ እንዲሆን ግንዛቤውን ከማሳደግ ባለፈ የዘር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
ወይዘሮ ሻሼ ሻጎ የተባሉ ነዋሪ በበኩላቸው፥ ኮሌጁ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር እያከናወነ ባለው ተግባር የሥራ ዕድል ማግኘታቸውን ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም በጥቃቅን የችርቻሮ ንግድ ሥራ ተሰማርቼ በማገኛት ጥቂት ገንዘብ ቤተሰብ ለማስተዳደር እቸገር ነበር ያሉት ወይዘሮ ሻሼ፣ አሁን ላይ በተፈጠረላቸው የሥራ ዕድል በሚያገኙት ገቢ ያለስጋት ኑሯቸውን እየመሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የወላይታ ሶዶ ግብርና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ የተሻሻሉ የግብርና አሰራርና ቴክኖሎጂዎችን ለማህበረሰቡ ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ ሥራውን ለማስፋፋት ግብ ጥሎ እየሰራ መሆኑም ታውቋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026