
አዲስ አበባ፤ግንቦት 4/2017 (ኢዜአ)፡-የአፍሪካ ህብረት የዘላቂ እዳ አስተዳደርን አስመልክቶ ያዘጋጀው ኮንፈረንስ ዛሬ በቶጎ ሎሜ መካሄድ ጀምሯል።
ኮንፈረንሱ እየተካሄደ የሚገኘው “የአፍሪካ የመንግስት የእዳ አስተዳደር አጀንዳ፤ዘላቂ የእዳ አስተዳደርን የሚያረጋግጡ ስትራቴጂዎችን መተግበር” በሚል መሪ ሀሳብ ነው።
በመክፈቻው ስነ ስርዓት ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽን ሞሰስ ቪላካቲ፣ የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ ክላቨር ጋቴቴ፣ የጋና ፕሬዝዳንት ጆን ድራማኒ ማህማ የአፍሪካ ሀገራት የፋይናንስ ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የአፍሪካ ፋይናንስ ተቋማት፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በአፍሪካ ወቅታዊ የእዳ ሁኔታ ላይ በመምከርም የሀገራት የዘላቂ እዳ አስተዳደር ተሞክሮ መለዋወጥ እና አፍሪካ በእዳ የጋራ አቋም ለመያዝ የሚያስችላት ምክረ ሀሳቦች ማቅረብ የኮንፈረንሱ ዋንኛ አላማ መሆኑን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው ያመለክታል።
በአህጉሪቷ ላለው የእዳ ቀውስ ምላሽ ለመስጠት አሁናዊ የዓለም የፋይናንስ መዋቅር መደረግ የሚገባቸውን ሪፎርሞች በተመለከተም ውይይት ይካሄዳል።
ዘላቂ የእዳ አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን አማራጭ የፋይናንስ ምንጮችን ማስፋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ምክክር ይደረጋል።
በአፍሪካ ዘላቂ የእዳ አስተዳደርን ለመፍጠር የሚያስችሉ ውጤታማ የእዳ አስተዳደር አማራጮችን በተመለከተ የመፍትሄ አማራጮች እንደሚቀርቡ ተገልጿል።
ውይይቱን ተከትሎ የአፍሪካ ሀገራት የእዳ አስተዳደር፣የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ማሻሻያ እና ዘላቂ የፋይናንስ አስተዳደርን አስመልክቶ የጋራ አቋም መግለጫ እንደሚያወጡ ይጠበቃል።
የአፍሪካ ህብረት የዘላቂ እዳ አስተዳደር ኮንፍረንስ እስከ ግንቦት 6 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026