የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የአፍሪካ ህብረት የዘላቂ እዳ አስተዳደር ላይ አህጉራዊ ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው

May 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 4/2017 (ኢዜአ)፡-የአፍሪካ ህብረት የዘላቂ እዳ አስተዳደርን አስመልክቶ ያዘጋጀው ኮንፈረንስ ዛሬ በቶጎ ሎሜ መካሄድ ጀምሯል።


ኮንፈረንሱ እየተካሄደ የሚገኘው “የአፍሪካ የመንግስት የእዳ አስተዳደር አጀንዳ፤ዘላቂ የእዳ አስተዳደርን የሚያረጋግጡ ስትራቴጂዎችን መተግበር” በሚል መሪ ሀሳብ ነው።


በመክፈቻው ስነ ስርዓት ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽን ሞሰስ ቪላካቲ፣ የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ ክላቨር ጋቴቴ፣ የጋና ፕሬዝዳንት ጆን ድራማኒ ማህማ የአፍሪካ ሀገራት የፋይናንስ ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የአፍሪካ ፋይናንስ ተቋማት፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።


በአፍሪካ ወቅታዊ የእዳ ሁኔታ ላይ በመምከርም የሀገራት የዘላቂ እዳ አስተዳደር ተሞክሮ መለዋወጥ እና አፍሪካ በእዳ የጋራ አቋም ለመያዝ የሚያስችላት ምክረ ሀሳቦች ማቅረብ የኮንፈረንሱ ዋንኛ አላማ መሆኑን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው ያመለክታል።


በአህጉሪቷ ላለው የእዳ ቀውስ ምላሽ ለመስጠት አሁናዊ የዓለም የፋይናንስ መዋቅር መደረግ የሚገባቸውን ሪፎርሞች በተመለከተም ውይይት ይካሄዳል።


ዘላቂ የእዳ አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን አማራጭ የፋይናንስ ምንጮችን ማስፋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ምክክር ይደረጋል።


በአፍሪካ ዘላቂ የእዳ አስተዳደርን ለመፍጠር የሚያስችሉ ውጤታማ የእዳ አስተዳደር አማራጮችን በተመለከተ የመፍትሄ አማራጮች እንደሚቀርቡ ተገልጿል።


ውይይቱን ተከትሎ የአፍሪካ ሀገራት የእዳ አስተዳደር፣የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ማሻሻያ እና ዘላቂ የፋይናንስ አስተዳደርን አስመልክቶ የጋራ አቋም መግለጫ እንደሚያወጡ ይጠበቃል።


የአፍሪካ ህብረት የዘላቂ እዳ አስተዳደር ኮንፍረንስ እስከ ግንቦት 6 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026