
አዲስ አበባ፤ግንቦት 4/2017 (ኢዜአ)፡-የአፍሪካ ህብረት የዘላቂ እዳ አስተዳደርን አስመልክቶ ያዘጋጀው ኮንፈረንስ ዛሬ በቶጎ ሎሜ መካሄድ ጀምሯል።
ኮንፈረንሱ እየተካሄደ የሚገኘው “የአፍሪካ የመንግስት የእዳ አስተዳደር አጀንዳ፤ዘላቂ የእዳ አስተዳደርን የሚያረጋግጡ ስትራቴጂዎችን መተግበር” በሚል መሪ ሀሳብ ነው።
በመክፈቻው ስነ ስርዓት ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽን ሞሰስ ቪላካቲ፣ የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ ክላቨር ጋቴቴ፣ የጋና ፕሬዝዳንት ጆን ድራማኒ ማህማ የአፍሪካ ሀገራት የፋይናንስ ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የአፍሪካ ፋይናንስ ተቋማት፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በአፍሪካ ወቅታዊ የእዳ ሁኔታ ላይ በመምከርም የሀገራት የዘላቂ እዳ አስተዳደር ተሞክሮ መለዋወጥ እና አፍሪካ በእዳ የጋራ አቋም ለመያዝ የሚያስችላት ምክረ ሀሳቦች ማቅረብ የኮንፈረንሱ ዋንኛ አላማ መሆኑን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው ያመለክታል።
በአህጉሪቷ ላለው የእዳ ቀውስ ምላሽ ለመስጠት አሁናዊ የዓለም የፋይናንስ መዋቅር መደረግ የሚገባቸውን ሪፎርሞች በተመለከተም ውይይት ይካሄዳል።
ዘላቂ የእዳ አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን አማራጭ የፋይናንስ ምንጮችን ማስፋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ምክክር ይደረጋል።
በአፍሪካ ዘላቂ የእዳ አስተዳደርን ለመፍጠር የሚያስችሉ ውጤታማ የእዳ አስተዳደር አማራጮችን በተመለከተ የመፍትሄ አማራጮች እንደሚቀርቡ ተገልጿል።
ውይይቱን ተከትሎ የአፍሪካ ሀገራት የእዳ አስተዳደር፣የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ማሻሻያ እና ዘላቂ የፋይናንስ አስተዳደርን አስመልክቶ የጋራ አቋም መግለጫ እንደሚያወጡ ይጠበቃል።
የአፍሪካ ህብረት የዘላቂ እዳ አስተዳደር ኮንፍረንስ እስከ ግንቦት 6 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026