የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ዲጂታል ቴክኖሎጂ አገልግሎትን በማቀላጠፍ የገቢ አቅምን ለማሳደግ ገንቢ ሚና እየተጫወተ ነው - ገቢዎች ሚኒስቴር

May 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፦ ዲጂታል ቴክኖሎጂ የአገልግሎት አሰጣጥን በማቀላጠፍ የገቢ አቅምን ለማሳደግ ገንቢ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ።

ተቋማት ዲጂታል ቴክኖሎጂን ገንብተው አገልግሎት አሰጣጣቸውን እንዲያቀላጥፉ መንግስት በርካታ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል፡፡

በዚህም በርካታ ተቋማት ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ለህብረተሰቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡

ከእነዚህ ተቋማት መካከል የገቢዎች ሚኒስቴርን ለአብነት ማንሳት ይቻላል።

በገቢዎች ሚኒስቴር የመረጃ፣ ቴክኖሎጂ ልማትና አስተደዳር ዳይሬክተር ኩራቱ ለማ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ሚኒስቴሩ የገቢ ግብር አሰባሰብ አቅምን የሚያሳድጉ የቴክኖሎጂ አሰራር ሥርዓቶች ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል።

ይህም በዘርፉ አገልግሎት አሰጣጡን በማቀላጠፍ ውጤቶች እንዲመዘገቡ እያስቻለ ይገኛል ብለዋል፡፡

የቴክኖሎጂና የኤሌክትሮኒክስ የገቢ ግብር ሥርዓቶች ተግበራዊ መደረግ ህገ-ወጥ ዝንባሌዎችን በመከላከል በኩል እያመጡ ያለውን ውጤት ለአብነት አንስተዋል።

ግብር ከፋዩ ባለበት ቦታ ሆኖ ክፍያ መፈጸም የሚችልበት ምቹ አጋጣሚ መፍጠሩንም ጨምረው አንስተዋል።

ቴክኖሎጂው በአሁን ወቅት 95 በመቶ የፌደራል ግብር ከፋዮች ግብራቸውን በዘመናዊና መንገድ እንዲከፍሉ አስችሏል ብለዋል።

የገቢ አሰባሰብ ሂደቱን ሙሉ ለሙሉ በዘመናዊ የቴክኖሎጂ ሥርዓት ለማከናወን ከባለድርሻ አካላትና ቴክኖሎጂ አልሚዎች ጋር በትብብር እየተሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል።

ኢዜአ ያነጋገራቸው ግብር ከፋዮች በበኩላቸው ቀደም ሲል የነበረው የግብር አሰባሰብ ሂደት በተለይ ለግብር ከፋዩ የተቀላጠፈ እንዳልነበር ተናግረዋል።

አቶ አሸናፊ አለሙ ቀደም ሲል የነበረው የግብር አሰባሰብ ሂደት በንግዱ ዘርፍ ለመሰማራት የማይጋብዝና ለእንግልትና ለወጪ የሚዳርግ እንደነበር አስታውሰዋል።

አሁን ላይ ግብርን በዘመናዊ መንገድ መክፈል የሚቻልበት አሰራር በመተግበሩ በቀላሉ መክፈል እንዳስቻላቸው ገልጸዋል።

ሌላው ግብር ከፋይ አቶ አለማየሁ ተክለማሪያም በበኩላቸው፤ የግብር አሰባሰብ ስርዓት ወደ ዘመናዊ መምጣቱ ግብር ከፋዩን የሚያነቃቃ ነው ብለዋል።

የግብር አከፋፈል ሂደቱ ፈጣንና ጊዜውን የዋጀ እንዲሆን ተደርጓል ያሉት ደግሞ ሌላኛው አስተያያት ሰጪ ፍቃዱ ድሪባ(ዶ/ር) ናቸው።

በመሆኑም ግብር ከፋዩ ግብሩን ወቅቱን ጠብቆ እንዲከፍል ማስቻሉን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025