የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

አርሶ አደሮች ምርቶቻቸውን በበለጠ ጥራትና ብዛት ለኢንዱስትሪ ፓርኮች እንዲያቀርቡ በማስቻል የተሻለ ገቢ እንዲያገኙ ይደረጋል

May 15, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፦ አርሶ አደሮች ምርቶቻቸውን በበለጠ ጥራትና ብዛት ለኢንዱስትሪ ፓርኮች እንዲያቀርቡ በማስቻል የተሻለ ገቢ እንዲያገኙ እንደሚሰራ የሲዳማ ክልል ኢንዱስረትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ።

ኮርፖሬሽኑ ከይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዱስረትሪ ፓርክ ባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል፡፡

የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊና የኮርፖሬሽኑ የቦርድ ሰብሳቢ አራርሶ ገረመው(ዶ/ር) አርሶ አደሮች ምርቶቻቸውን በበለጠ ጥራትና ብዛት ለኢንዱስትሪ ፓርኮች እንዲያቀርቡ በማስቻል የተሻለ ገቢ እንዲያገኙ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

ለፓርኩ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን በግብዓትነት የሚያቀርቡ አርሶ አደሮች ትስስር በማጠናከር ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል ብለዋል።


በእስካሁኑ ሂደት ከፓርኩ ጋር ትስስር የተፈጠረላቸው አርሶ አደሮች ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሰው ምርቶቻቸውን በበለጠ ጥራትና ብዛት በማቅረብ የተሻለ ገቢ ማግኘት እንዲችሉ ይደረጋል ብለዋል፡፡

በቀጣይ ሶስት ወራት ከፓርኩ ጋር ትስስር የተፈጠረላቸው 40ሺህ አርሶ አደሮች የምርቶቻቸውን ጥራትና ብዛት ማሳደግ የሚያስችላቸውን ሥልጠና እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል።

ሥልጠናው በምርት ሂደት፣ በአሰባሰብና አያያዝ ላይ የዘመነ አሰራር እንዲከተሉ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ያለመ መሆኑንም ተናግረዋል።


የክልሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኃይሉ ዬቴራ፤ ፓርኩ ሥራ ከጀመረ አንስቶ በግብዓት ትስስርና በሥራ ዕድል ፈጠራ አርሶ አደሮችንና ወጣቶችን ተጠቃሚ ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰዋል።

ከሶስት ዓመት በፊት በፓርኩ የግብዓት ሰንሰለት ውስጥ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ትስስር የተፈጠረላቸው አርሶ አደሮች 36ሺህ እንደነበሩ ጠቅሰው በአሁን ወቅት ቁጥራቸውን 136ሺህ መድረሱን ተናግረዋል፡፡

በአሁን ወቅት በፓርኩ አቮካዶ፣ ወተት፣ ማርና ቡና የሚያቀነባብሩ ስምንት ኩባንያዎች በሥራ ላይ መሆናቸውን አንስተው ግብዓት የሚያቀርቡ አርሶ አደሮች ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የተሻለ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሥልጠናው እንደሚያግዛቸው አስረድተዋል፡፡

በምክክር መድረኩ የክልል፣ የዞን እና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም የኮርፖሬሽኑ፣ የኢንዱስትሪ ፓርኩና የኩባንያ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026