አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2017(ኢዜአ)፦ በቤተሰብ ደረጃ ኢኮኖሚን በማሳደግ ወደ ተሻለ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅባቸው የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስገነዘበ።
የቤተሰብ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ32ኛ ጊዜ በኢትየጵያ ደግሞ ለሶስተኛ ጊዜ "የተሻሻለ የቤተሰብ ሥራና ገቢ ለሀገር ኢኮኖሚ" በሚል መሪ ሀሳብ ተከብሯል።
የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የቤተሰብ ኢኮኖሚ አቅምን ማሻሻል እና ጥሪት ግንባታን መደገፍ ይገባል።
በተለይም የፌዴራልና የክልል አስፈጻሚ አካላት የቤተሰብ የክህሎት ክፍተትን በመሙላት፣ የመስሪያ ቦታ እና የፋይናንስ አቅርቦት ችግር ለማቃለል በቁርጠኝነት እንዲሰሩም ጠይቀዋል።
በሀገሪቱ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል አንዱ የቤተሰብ ደህንነት ጥበቃ እና ጥሪት ግንባታ በመሆኑ በዘርፉ ለውጥ ለማምጣት ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።
ማንኛውም ቤተሰብ በሀገራዊ ብልጽግና እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አዎንታዊ ሚና እንዲኖረው ሁኔታዎችን ማመቻቸት እንደሚገባም ነው የጠቆሙት።
ቤተሰብን ከድህነትና ከተረጂነት በማላቀቅ ወደ ምርታማነት እና የተሻለ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አንስተዋል።
ቤተሰብ በተነቃቃ የስራ ባህል ጥሪት በማፍራት፣ ኢኮኖሚውን በመገንባትና ለቀጣዩ ትውልድ ጭምር በማሸጋገር ለማህበረሰብ ሁለንተናዊ ለውጥ የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025