
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2017(ኢዜአ)፦ በቤተሰብ ደረጃ ኢኮኖሚን በማሳደግ ወደ ተሻለ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅባቸው የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስገነዘበ።
የቤተሰብ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ32ኛ ጊዜ በኢትየጵያ ደግሞ ለሶስተኛ ጊዜ "የተሻሻለ የቤተሰብ ሥራና ገቢ ለሀገር ኢኮኖሚ" በሚል መሪ ሀሳብ ተከብሯል።
የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የቤተሰብ ኢኮኖሚ አቅምን ማሻሻል እና ጥሪት ግንባታን መደገፍ ይገባል።
በተለይም የፌዴራልና የክልል አስፈጻሚ አካላት የቤተሰብ የክህሎት ክፍተትን በመሙላት፣ የመስሪያ ቦታ እና የፋይናንስ አቅርቦት ችግር ለማቃለል በቁርጠኝነት እንዲሰሩም ጠይቀዋል።
በሀገሪቱ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል አንዱ የቤተሰብ ደህንነት ጥበቃ እና ጥሪት ግንባታ በመሆኑ በዘርፉ ለውጥ ለማምጣት ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።
ማንኛውም ቤተሰብ በሀገራዊ ብልጽግና እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አዎንታዊ ሚና እንዲኖረው ሁኔታዎችን ማመቻቸት እንደሚገባም ነው የጠቆሙት።
ቤተሰብን ከድህነትና ከተረጂነት በማላቀቅ ወደ ምርታማነት እና የተሻለ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አንስተዋል።
ቤተሰብ በተነቃቃ የስራ ባህል ጥሪት በማፍራት፣ ኢኮኖሚውን በመገንባትና ለቀጣዩ ትውልድ ጭምር በማሸጋገር ለማህበረሰብ ሁለንተናዊ ለውጥ የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026