
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2017(ኢዜአ)፦ በቤተሰብ ደረጃ ኢኮኖሚን በማሳደግ ወደ ተሻለ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅባቸው የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስገነዘበ።
የቤተሰብ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ32ኛ ጊዜ በኢትየጵያ ደግሞ ለሶስተኛ ጊዜ "የተሻሻለ የቤተሰብ ሥራና ገቢ ለሀገር ኢኮኖሚ" በሚል መሪ ሀሳብ ተከብሯል።
የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የቤተሰብ ኢኮኖሚ አቅምን ማሻሻል እና ጥሪት ግንባታን መደገፍ ይገባል።
በተለይም የፌዴራልና የክልል አስፈጻሚ አካላት የቤተሰብ የክህሎት ክፍተትን በመሙላት፣ የመስሪያ ቦታ እና የፋይናንስ አቅርቦት ችግር ለማቃለል በቁርጠኝነት እንዲሰሩም ጠይቀዋል።
በሀገሪቱ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል አንዱ የቤተሰብ ደህንነት ጥበቃ እና ጥሪት ግንባታ በመሆኑ በዘርፉ ለውጥ ለማምጣት ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።
ማንኛውም ቤተሰብ በሀገራዊ ብልጽግና እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አዎንታዊ ሚና እንዲኖረው ሁኔታዎችን ማመቻቸት እንደሚገባም ነው የጠቆሙት።
ቤተሰብን ከድህነትና ከተረጂነት በማላቀቅ ወደ ምርታማነት እና የተሻለ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አንስተዋል።
ቤተሰብ በተነቃቃ የስራ ባህል ጥሪት በማፍራት፣ ኢኮኖሚውን በመገንባትና ለቀጣዩ ትውልድ ጭምር በማሸጋገር ለማህበረሰብ ሁለንተናዊ ለውጥ የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ተናግረዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026