
ደብረ ማርቆስ፤ግንቦት 10/2017(ኢዜአ)፦አሲዳማ መሬትን በኖራ በማከም ለሰብል ልማት በማዋል የተሻለ ምርት እያገኙ መሆኑን በምስራቅ ጎጃም ዞን ኢዜአ ያነጋገራቸው አርሶ አደሮች ገለጹ።
በዞኑ የ2017/18 የምርት ዘመን ከ248 ሄክታር በላይ መሬት በኖራ በማከም ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑም ተመላክቷል።
በምስራቅ ጎጃም ዞን የማቻከል ወረዳ አርሶ አደር በቃሉ ነጮ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ በአሲድ የተጠቃ መሬታቸውን በማከም መዝራት ከጀመሩ ሶስት ዓመት ሆኗቸዋል።
በዚህም በሄክታር በፊት ያገኙት ከነበረው ከስድስት ኩንታል በላይ ብልጫ ያለው ምርት ማግኘታቸውን ገልጸው፥ በዚህ ዓመት ይበልጥ ለማስፋት እቅድ እንዳላቸው ተናግረዋል።
ሌላው በዞኑ የአነደድ ወረዳ አርሶ አደር አስማረ ምናሴ በበኩላቸው፥ ከአንድ ሄክታር በላይ የእርሻ ማሳቸው በአሲድ በመጠቃቱ የምርት መጠኑ ቀንሶ መቆየቱን አስታውሰው፥ አሁን ላይ በኖራ ታክሞ ከፍተኛ ለውጥ አሳይቷል ብለዋል።
በዚህ ዓመት በግብርና በኩል የቀረበላቸውን ኖራ ከግማሽ ሄክታር በላይ የእርሻ ማሳቸው ላይ ቀድመው ከአፈሩ ጋር የማዋሃድ ስራ በመስራት ለዘር ማዘጋጀታቸውንም አስረድተዋል።
የምስራቅ ጎጃም ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ እንቢአለ አለኸኝ፤በ2017/18 የምርት ዘመን በዞኑ ከ248 ሄክታር በላይ አሲዳማ መሬት በኖራ በማከም ምርታማነቱን ለማሻሻል እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ለዚህም ከ64 ሺህ ኩንታል በላይ ኖራ ለማቅረብ ታቅዶ እስካሁን ከ18 ሺህ 500 ኩንታል በላይ ማቅረብ መቻሉን ገልጸዋል።
በመጪው የመኸር ምርት ዘመን አዳዲስ አሰራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የግብርናውን ምርታማነት በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል የተያዘውን ግብ ለማሳካት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
በዞኑ 2017/18 የምርት ዘመን ከ25 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማምረት ታቅዶ የእርሻና የዘር ዝግጅት በመደረግ ላይ መሆኑ ታውቋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026