
ደብረ ማርቆስ፤ግንቦት 10/2017(ኢዜአ)፦አሲዳማ መሬትን በኖራ በማከም ለሰብል ልማት በማዋል የተሻለ ምርት እያገኙ መሆኑን በምስራቅ ጎጃም ዞን ኢዜአ ያነጋገራቸው አርሶ አደሮች ገለጹ።
በዞኑ የ2017/18 የምርት ዘመን ከ248 ሄክታር በላይ መሬት በኖራ በማከም ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑም ተመላክቷል።
በምስራቅ ጎጃም ዞን የማቻከል ወረዳ አርሶ አደር በቃሉ ነጮ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ በአሲድ የተጠቃ መሬታቸውን በማከም መዝራት ከጀመሩ ሶስት ዓመት ሆኗቸዋል።
በዚህም በሄክታር በፊት ያገኙት ከነበረው ከስድስት ኩንታል በላይ ብልጫ ያለው ምርት ማግኘታቸውን ገልጸው፥ በዚህ ዓመት ይበልጥ ለማስፋት እቅድ እንዳላቸው ተናግረዋል።
ሌላው በዞኑ የአነደድ ወረዳ አርሶ አደር አስማረ ምናሴ በበኩላቸው፥ ከአንድ ሄክታር በላይ የእርሻ ማሳቸው በአሲድ በመጠቃቱ የምርት መጠኑ ቀንሶ መቆየቱን አስታውሰው፥ አሁን ላይ በኖራ ታክሞ ከፍተኛ ለውጥ አሳይቷል ብለዋል።
በዚህ ዓመት በግብርና በኩል የቀረበላቸውን ኖራ ከግማሽ ሄክታር በላይ የእርሻ ማሳቸው ላይ ቀድመው ከአፈሩ ጋር የማዋሃድ ስራ በመስራት ለዘር ማዘጋጀታቸውንም አስረድተዋል።
የምስራቅ ጎጃም ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ እንቢአለ አለኸኝ፤በ2017/18 የምርት ዘመን በዞኑ ከ248 ሄክታር በላይ አሲዳማ መሬት በኖራ በማከም ምርታማነቱን ለማሻሻል እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ለዚህም ከ64 ሺህ ኩንታል በላይ ኖራ ለማቅረብ ታቅዶ እስካሁን ከ18 ሺህ 500 ኩንታል በላይ ማቅረብ መቻሉን ገልጸዋል።
በመጪው የመኸር ምርት ዘመን አዳዲስ አሰራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የግብርናውን ምርታማነት በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል የተያዘውን ግብ ለማሳካት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
በዞኑ 2017/18 የምርት ዘመን ከ25 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማምረት ታቅዶ የእርሻና የዘር ዝግጅት በመደረግ ላይ መሆኑ ታውቋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026