
ጅማ፤ ግንቦት 11/2017(ኢዜአ)፡- የራስን አቅም በማጎልበትና ምርታማነትን ይበልጥ በማሳደግ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ገለጹ።

የክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የዓመቱ የሌማት ትሩፋት መርሃግብር፣ የስነ ምግብና የሰቆጣ ቃልኪዳን ስራዎችን በመገምገም አቅጣጫ የሚያስቀምጥ መድረክ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ነው።
አቶ አደም በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ ያለንን ሰፊ ለም መሬት፣ የሰው ሀብት እና የውሃ ሀብት በመጠቀም የግብርና አቅማችንን በማጎልበት ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር በመሰራት ላይ ይገኛል ብለዋል።
የራስን አቅም አጎልብቶ ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ በማሳደግ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የተለያዩ የግብርና ኢንሼቲቮች ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም በስንዴ፣ በሩዝ፣ በማር እና በሌሎችም የግብርና ዘርፎች ያተኮሩ መሆኑን ገልጸዋል።
በመድረኩ ላይ የፌደራል፣ የክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ከፍተኛ የአመራር አባላት ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026