ጅማ፤ ግንቦት 11/2017(ኢዜአ)፡- የራስን አቅም በማጎልበትና ምርታማነትን ይበልጥ በማሳደግ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ገለጹ።
የክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የዓመቱ የሌማት ትሩፋት መርሃግብር፣ የስነ ምግብና የሰቆጣ ቃልኪዳን ስራዎችን በመገምገም አቅጣጫ የሚያስቀምጥ መድረክ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ነው።
አቶ አደም በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ ያለንን ሰፊ ለም መሬት፣ የሰው ሀብት እና የውሃ ሀብት በመጠቀም የግብርና አቅማችንን በማጎልበት ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር በመሰራት ላይ ይገኛል ብለዋል።
የራስን አቅም አጎልብቶ ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ በማሳደግ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የተለያዩ የግብርና ኢንሼቲቮች ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም በስንዴ፣ በሩዝ፣ በማር እና በሌሎችም የግብርና ዘርፎች ያተኮሩ መሆኑን ገልጸዋል።
በመድረኩ ላይ የፌደራል፣ የክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ከፍተኛ የአመራር አባላት ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025