
ጅማ፤ ግንቦት 11/2017(ኢዜአ)፡- የራስን አቅም በማጎልበትና ምርታማነትን ይበልጥ በማሳደግ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ገለጹ።

የክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የዓመቱ የሌማት ትሩፋት መርሃግብር፣ የስነ ምግብና የሰቆጣ ቃልኪዳን ስራዎችን በመገምገም አቅጣጫ የሚያስቀምጥ መድረክ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ነው።
አቶ አደም በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ ያለንን ሰፊ ለም መሬት፣ የሰው ሀብት እና የውሃ ሀብት በመጠቀም የግብርና አቅማችንን በማጎልበት ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር በመሰራት ላይ ይገኛል ብለዋል።
የራስን አቅም አጎልብቶ ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ በማሳደግ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የተለያዩ የግብርና ኢንሼቲቮች ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም በስንዴ፣ በሩዝ፣ በማር እና በሌሎችም የግብርና ዘርፎች ያተኮሩ መሆኑን ገልጸዋል።
በመድረኩ ላይ የፌደራል፣ የክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ከፍተኛ የአመራር አባላት ተገኝተዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026