ሰመራ፤ ግንቦት 12/2017 (ኢዜአ) ፡-የፋይዳ ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ መሆናችን ፈጣንና ቀጣይነት ያለው አገልግሎት ማግኘት የሚያስችለን ነው ሲሉ በሠመራና አካባቢው የሚገኙ የመታወቂያው ተመዝጋቢዎች ተናገሩ።
በሠመራ ከተማ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መዝገባ በንቅናቄ መልክ በመከናወን ላይ ይገኛል።
በምዝገባ ሂደት ላይ ኢዜአ ካነጋገራቸው ተመዝጋቢዎች መካከል የዱብቲ ከተማ ነዋሪ አቶ ሳኒ አህመድ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚሰሩ የማጭበርበር ወንጀሎችን ለመከላከል ጥቅሙ የጎላ ነው ብለዋል ።
ሌላዋ የሠመራ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ሶፊያ አደም በበኩላቸው የብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት መሆን ጥቅሙ ብዙ መሆኑን በመረዳታቸው ለመመዝገብ መምጣታቸውን አብራርተዋል።
የፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ማግኘታችው እንደፈለጉ ተንቀሳቅሰው ለመስራትና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት እንደሚረዳቸው የገለጹት ደግሞ የዱብቲ ከተማ ነዋሪ አቶ ማህሙድ ዓሊ ናቸው።
"ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎቶችን በአንድ ላይ ለማግኘት የሚያችለን ነው" ያሉት ደግሞ የሠመራ ከተማ ነዋሪ አቶ ሁሴን መሐመድ ናቸው።
በኢትዮ ቴሌኮም የሰሜን ምስራቅ ምስራቅ ሰመራ ሪጅን የሽያጭ ክፍል ኀላፊ አቶ ሃጎስ ወልደጊዮርስ በበኩላቸው ፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ የኢትዮጵያን የዲጂታል አለምን ጉዞ የሚያሳልጥ ቁልፍ መሣሪያ ነው ብለዋል።
እንደ አገር እየተከናወነ ያለውን የዲታላይዜሽን ጉዞ ለማፋጠንና የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚረዳ መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህም አገልግሎቱ በተለያዩ ደረጃ የሚከናወኑ ማጭበርበሮችን የሚከላከል በመሆኑ በክልሉ የተለያዩ ማዕከሎች እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025