የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የፋይዳ ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፈጣንና ቀጣይነት ያለው አገልግሎት ማግኘት የሚያስችለን ነው - ተመዝጋቢዎች

May 21, 2025

IDOPRESS

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2017 (ኢዜአ) ፡-የፋይዳ ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ መሆናችን ፈጣንና ቀጣይነት ያለው አገልግሎት ማግኘት የሚያስችለን ነው ሲሉ በሠመራና አካባቢው የሚገኙ የመታወቂያው ተመዝጋቢዎች ተናገሩ።

በሠመራ ከተማ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መዝገባ በንቅናቄ መልክ በመከናወን ላይ ይገኛል።

በምዝገባ ሂደት ላይ ኢዜአ ካነጋገራቸው ተመዝጋቢዎች መካከል የዱብቲ ከተማ ነዋሪ አቶ ሳኒ አህመድ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚሰሩ የማጭበርበር ወንጀሎችን ለመከላከል ጥቅሙ የጎላ ነው ብለዋል ።


ሌላዋ የሠመራ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ሶፊያ አደም በበኩላቸው የብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት መሆን ጥቅሙ ብዙ መሆኑን በመረዳታቸው ለመመዝገብ መምጣታቸውን አብራርተዋል።


የፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ማግኘታችው እንደፈለጉ ተንቀሳቅሰው ለመስራትና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት እንደሚረዳቸው የገለጹት ደግሞ የዱብቲ ከተማ ነዋሪ አቶ ማህሙድ ዓሊ ናቸው።


"ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎቶችን በአንድ ላይ ለማግኘት የሚያችለን ነው" ያሉት ደግሞ የሠመራ ከተማ ነዋሪ አቶ ሁሴን መሐመድ ናቸው።


በኢትዮ ቴሌኮም የሰሜን ምስራቅ ምስራቅ ሰመራ ሪጅን የሽያጭ ክፍል ኀላፊ አቶ ሃጎስ ወልደጊዮርስ በበኩላቸው ፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ የኢትዮጵያን የዲጂታል አለምን ጉዞ የሚያሳልጥ ቁልፍ መሣሪያ ነው ብለዋል።


እንደ አገር እየተከናወነ ያለውን የዲታላይዜሽን ጉዞ ለማፋጠንና የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚረዳ መሆኑን አብራርተዋል።

በዚህም አገልግሎቱ በተለያዩ ደረጃ የሚከናወኑ ማጭበርበሮችን የሚከላከል በመሆኑ በክልሉ የተለያዩ ማዕከሎች እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026