
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2017 (ኢዜአ) ፡-የፋይዳ ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ መሆናችን ፈጣንና ቀጣይነት ያለው አገልግሎት ማግኘት የሚያስችለን ነው ሲሉ በሠመራና አካባቢው የሚገኙ የመታወቂያው ተመዝጋቢዎች ተናገሩ።
በሠመራ ከተማ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መዝገባ በንቅናቄ መልክ በመከናወን ላይ ይገኛል።
በምዝገባ ሂደት ላይ ኢዜአ ካነጋገራቸው ተመዝጋቢዎች መካከል የዱብቲ ከተማ ነዋሪ አቶ ሳኒ አህመድ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚሰሩ የማጭበርበር ወንጀሎችን ለመከላከል ጥቅሙ የጎላ ነው ብለዋል ።

ሌላዋ የሠመራ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ሶፊያ አደም በበኩላቸው የብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት መሆን ጥቅሙ ብዙ መሆኑን በመረዳታቸው ለመመዝገብ መምጣታቸውን አብራርተዋል።

የፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ማግኘታችው እንደፈለጉ ተንቀሳቅሰው ለመስራትና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት እንደሚረዳቸው የገለጹት ደግሞ የዱብቲ ከተማ ነዋሪ አቶ ማህሙድ ዓሊ ናቸው።

"ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎቶችን በአንድ ላይ ለማግኘት የሚያችለን ነው" ያሉት ደግሞ የሠመራ ከተማ ነዋሪ አቶ ሁሴን መሐመድ ናቸው።

በኢትዮ ቴሌኮም የሰሜን ምስራቅ ምስራቅ ሰመራ ሪጅን የሽያጭ ክፍል ኀላፊ አቶ ሃጎስ ወልደጊዮርስ በበኩላቸው ፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ የኢትዮጵያን የዲጂታል አለምን ጉዞ የሚያሳልጥ ቁልፍ መሣሪያ ነው ብለዋል።

እንደ አገር እየተከናወነ ያለውን የዲታላይዜሽን ጉዞ ለማፋጠንና የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚረዳ መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህም አገልግሎቱ በተለያዩ ደረጃ የሚከናወኑ ማጭበርበሮችን የሚከላከል በመሆኑ በክልሉ የተለያዩ ማዕከሎች እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026