አዲስ አበባ፤ ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዲጂታል ኢኮኖሚ ለምታደርገው ንቁ ተሳትፎ ፋይዳ ወሳኝ ሚና እንዳለው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ዲጂታል ማንነት ላይ ትኩረቱን ያደረገው አይዲ ፎር አፍሪካ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባዔ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ዲጂታል ማንነትን ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያድርግ ዘመናዊ፣ አካታች እና መሠረታዊ የዲጂታል ማንነት መለያ ስርዓት መዘረጋቷን ጠቁመዋል።
ፋይዳ ካርድ ብቻ ሳይሆን ልዩ የሆኑ ቁጥሮችን የያዘና ማንነት የሚረጋገጥበት መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እስካሁን ለ15 ሚሊዮን ዜጎች ተደራሽ መደረጉን ጠቁመዋል፡፡
ዜጎች በዲጂታል ኢኮኖሚ ዘርፍ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ፋይዳ ትልቅ ዕድል መፍጠሩን ገልጸው፤ ለሁሉም ዘርፎች ምቹ መደላደል ማድረጉንም ጠቁመዋል፡፡
ፋይዳን ለፋይናንስ፣ ጤና፣ ትምህርት፣ ቴሌኮም፣ የህዝብ አገልግሎቶች ከማህበራዊ ዋስትና ጋር በማስተሳሰር ተዓማኒ የሆነ መደላድል ለህዝቡ ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ፋይዳ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ፈጣን የሆነ ዲጂታል ኢኮኖሚ ለመገንባት ትልቅ አበርክቶ እንዳለው ጠቁመው፤ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና እውን ለማድረግ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወትም ተናግረዋል፡፡
የዲጂታል ማንነት መለያ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ወሳኝ መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለዓላማው በህብረት በመሰለፍ የአፍሪካን እምቅ አቅም ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
ኢትዮጵያ ከኮንፈረንስ ማዕከልነት ባሻገር የራሷ ማንነት ያላት ናት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እጅግ ውብ በሆኑ የአዲስ አበባ ጎዳናዎች እንዲሁም ከመልክዓ ምድሯ ልምድ መውሰድ የሚቻል ስለመሆኑም አንስተዋል፡፡
ተሳታፊዎች ወደ መጡበት አካባቢ ሲመለሱም ሁሉም ሰው አስተማማኝ የዲጂታል ማንነት መለያ እንዲኖረው በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባም አመልክተዋል፡፡
በመድረኩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘው ተሻገር፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ አገራት አምባሳደሮችና የአለም አቀፍ ድርጅት ተወካዮች ታድመዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025