የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከጎረቤት አገሮች ጋር የጋራ ልማትና ትስስርን አጠናክሯል

May 26, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 16/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከጎረቤት አገሮች ጋር የጋራ ልማትና ትስስርን ማጠናከሩን ተገለጸ።


በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ዳሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሽብሩ ማሞ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በዲፕሎማሲው መስክ በዓለም አቀፍ መድረክ እውቅና እና ተቀባይነት ያገኘ መሆኑን አስረድተዋል።


የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ለጎረቤት አገሮች ቅድሚያ የሚሰጥ እንደመሆኑ የጋራ ተጠቃሚነትና ቀጣናዊ ትስስርን የበለጠ ለማጠናከር በመሰረተ ልማት፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ በትብብር እየሰራች እንደምትገኝ ተናግረዋል።


በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጭነት ከስድስት ዓመት በፊት በተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከጎረቤት አገሮች ጋር በቅርበት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።


ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለጎረቤት አገሮች ችግኝ በመስጠት፣ በመትከልና ልምድ በማካፈል ትስስርን ለማጠናከር ከሰራችው ጠንካራ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ስራዎች ውስጥ ተጠቃሽ መሆኑን ጠቅሰዋል።


በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከጎረቤት አገሮች ጋር አብሮ የመልማት፣ የመበልጸግ፣ የተፈጥሮ ሃብትን በዘላቂነት በመጠበቅ በፍትሃዊነት የመጠቀም አቋሟን ያጠናከረችበትና በተሞክሮነት የተወሰደ መሆኑን ገልጸዋል።


የአየር ንብረት ለውጥን በዘላቂነት ለመከላከልና የተፈጥሮ ሃብትን ለመጠበቅ በመርሃ ግብሩ ያስመዘገበቻቸውን ውጤቶች በዓለም አቀፍ መድረኮች ልምዷን ማካፈሏንም ነው አምባሳደር ሽብሩ የገለጹት።


በየዓመቱ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል ያስመዘገበችው አስደናቂ ውጤት በዓለም አቀፍ መድረክ እውቅናን እንዳገኘ አስታውሰዋል።


በተለያየ የዓለም አገራት የሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች መርሃ ግብሩን የበለጠ ለማስፋትና ለማስተዋወቅ በትኩረት እየሰሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል።


የጎረቤት አገሮች ከኢትዮጵያ ልምድ በመውሰድ ችግኝ እንዲተክሉ መነሳሳትን የፈጠረ በጎ ተጽዕኖ መፍጠሩን ገልጸዋል።


በግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሃብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም መሪ ስራ አስፈጻሚ ፋኖሴ መኮንን በበኩላቸው፥ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተጎዳ መሬት እንዲያገግም፣ የመሬት እርጥበታማነት እንዲጨምር፣ የውሃ አካላት በመጠን እንዲጨምር ማድረጉን ዘርዝረዋል።


እንደ መሪ ስራ አስፈጻሚው ገለጻ፥በመርሃ ግብሩ 40 በመቶ የደንና 60 በመቶ የፍራፍሬ፣የእንስሳት መኖ፣ የአፈር ለምነትና ጤንነትን የሚጠብቁ ችግኞችን በመትከል ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል።


ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና እንክብካቤ ልምድ በማካፈል ከጎረቤት አገሮች ጋር በትብብር የመልማት ጽኑ ፍላጎቷን ያሳየችበት እንደሆነም ተናግረዋል።


በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ ችግኞች የታችኞቹ ተፋሰስ አገራት በጎርፍ አደጋ እንዳይጠቁ የራሱን አስተዋጽኦ እያደረገ እንደሚገኝም ተናግረዋል።


ለ2017 የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከሰባት ነጥብ አምስት ቢሊዮን በላይ ችግኝ ዝግጅት መደረጉን አቶ ፋኖሴ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026