የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በከተማው ከ3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እየተገነቡ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው

May 26, 2025

IDOPRESS

አምቦ፤ግንቦት 16/2017(ኢዜአ)፦በአምቦ ከተማ በ2017 በጀት ዓመት ከ3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እየተገነቡ የሚገኙ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የአምቦ ከተማ አስተዳደር ገለጸ።


የአምቦ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ተስፋዬ ደገፋ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ በበጀት ዓመቱ በከተማው የህዝቡን የልማት ጥያቄ የሚመልሱ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች እየተሰሩ ነው።


በከተማዋ እየተከናወኑ ካሉት የመሰረተ ልማት ግንባታዎች መካከል 28 ኪሎ ሜትር መንገድ፣የመንገድ ዳር መብራት፣የፍሳሽ ማስወገጃ ቦይ፣ የንፁህ መጠጥ ውሃ፣ የኮሪደር ልማት ስራዎች እና ሌሎችም ይገኙበታል ብለዋል።


ከተማዋን አቋርጦ የሚያልፈው መንገድ ጠባብ በመሆኑ በከተማዋ የትራፊክ ፍሰት ላይ ጫና ሲያደርግ መቆየቱን ገልጸው፥ ችግሩን ለመፍታትም ዋናውን መንገድ የማስፋት እና የውስጥ ለውስጥ መንገድ ግንባታ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።


በከተማው በከብት ማደለብ፤ በዶሮ እርባታ፣ በወተት ላምና በዓሳ እርባታ እንዲሁም በሌሎች የኢኒሼቲቭ ስራዎች ለተሰማሩ አካላት የሼድ ግንባታ ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል።


በከተማዋ ያለው የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ሽፋን እስካሁን 90 በመቶ መድረሱን አንስተው፥ የከተማዋ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ደግሞ 89 በመቶ መሆኑን አስረድተዋል።


በከተማው እየተገነቡ ያሉት መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች እስካሁን ከ9 ሺህ 300 ለሚበልጡ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን አመልክተዋል።


እየተከናወነ በሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራም የመንገድ ዳር ማስዋብ፣ የፍሳሽ ማስወገጃ ቦይ፣የተለያዩ አደባባዮችን ጨምሮ መዝናኛ ቦታዎች እና ሌሎች የልማት ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ጠቁመዋል።


በከተማው በሰፈነው ሰላም በሃገር ውስጥና በውጭ ያሉ ባለሃብቶች ወደ ከተማው መጥተው ኢንቨስት እንዲያርጉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡


የአምቦ ከተማ ነዋሪ ወጣት አበበ ገመቹ በበኩሉ፥ በከተማው አስተዳደር እና በሕብረተሰቡ ተሳትፎ እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎች ህዝቡን ተጠቃሚ እያደረጉ በመሆናቸው የድርሻውን እንደሚወጣም ተናግሯል፡፡


ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ባይሳ ተሾመ በበኩሉ፥ ከለውጡ ወዲህ የአምቦ ከተማ ህዝብ ጥያቄ ተራ በተራ እየተመለሰ ስለሆነ ህብረተሰቡም የተለመደ ትብብሩን እያደረገ ነው ብለዋል።


የከተማው ኮሪደር ልማት ከሌሎች በክልሉ ከሚገኙ ከተሞች አንፃር ሲታይ ቀሪ ስራዎች ቢኖሩም የተጀመሩ ተግባራት ግን አበረታች መሆናቸውን የገለፁት ደግሞ ሌላኛዋ የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ ብልብሉ በሪሶ ናቸው።


ሕብረተሰቡ እያደረገ ያለው ድጋፍ ለሌሎች ምሳሌ ሊሆን እንደሚችል ገልፀው እርሳቸውም የድርሻቸውን እንደሚወጡም ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026