
አዲስ አበባ፤ግንቦት 16/2017(ኢዜአ)፦ የብራዚል አፍሪካ የግብርና ዘርፍ ጉባኤ ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ከብራዚል ጋር ያላትን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ያስቻለ መሆኑን በብራዚል የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ገለፁ።
በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስን ጥሩነህ የተመራ ልዑክ በምግብ ዋስትና፣ ረሃብን በመዋጋት እና በገጠር ልማት አጀንዳዎች ላይ ባተኮረው ሁለተኛው የብራዚልና አፍሪካ ጉባኤ ላይ የተሳተፈ ሲሆን በብራዚልም ጉብኝቶችን አድርጓል።
የልዑኩን ቆይታ አስመልክቶ በብራዚል የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸውም ልዑክ ቡድኑ የብራዚል አፍሪካ የግብርና ዘርፍ ላይ ያተኮረ ጉባኤ ላይ መሳተፉን ተናግረዋል።
ከጉባኤው ጎን ለጎን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከብራዚል ምክትል ፕሬዝዳንት ጋር ግብርናን ጨምሮ በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቱሪዝም እና በአቪዬሽን ዘርፍ ያሉትን ግንኙነት ማሳደግ የሚያስችል ውይይት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።
ጉባኤው ብራዚልና አፍሪካ በግብርናው ዘርፍ በጋራ ለመስራት ልምድ በመለዋወጥ ረገድ እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ያተኮረ ስኬታማ መሆኑን ተረናግረዋል።
ከጉባኤው ጎን ለጎን የሀገሪቱን የግብርና ዘርፍ ተግባራት የመስክ ምልከታ መደረጉን ገልጸው፤ በዚህም ልምድ የተወሰደበት መሆኑን አምባሳደሩ አንስተዋል።
በርካታ ተሞክሮዎች የተገኙበት መሆኑን ም ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ ከብራዚል ጋር ያላትን የግብርና ዘርፍ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚያስችል እንደሆነ አስረድተዋል።
በጉባኤው ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ያስመዘገበቻቸውን ስኬቶች ለአፍሪካ ሀገራት እና ለብራዚል ማጋራቷን አምባሳደሩ ገልፀዋል።
በአረንጓዴ ልማት፣ በሌማት ትሩፋት፣ በስንዴ ምርትና ምርታማነት የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማጋራት መቻሉንም ጠቅሰዋል።
በግብርና ዘርፍ ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል የሁለትዮሽ የግብርና ትብብር ስምምነት መፈረሙንም አንስተዋል።
ጉባኤው እና ጉብኝቱ ለሀገራችን ግብርና ዘርፍ ተሞክሮ የተወሰደበት በተለይ ግብርና በቴክኖሎጂ ሲታገዝ የላቀ ለውጥ እንደሚያመጣ መገንዘብ የታቸለበት ነው ብለዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026