የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የብራዚል አፍሪካ የግብርና ዘርፍ ጉባኤ ኢትዮጵያ በዘርፉ ከብራዚል ጋር ያላትን ትብብር ያጠናከረ ነው -‎ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ

May 26, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 16/2017(ኢዜአ)፦ የብራዚል አፍሪካ የግብርና ዘርፍ ጉባኤ ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ከብራዚል ጋር ያላትን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ያስቻለ መሆኑን በብራዚል የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ገለፁ።

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስን ጥሩነህ የተመራ ልዑክ በምግብ ዋስትና፣ ረሃብን በመዋጋት እና በገጠር ልማት አጀንዳዎች ላይ ባተኮረው ሁለተኛው የብራዚልና አፍሪካ ጉባኤ ላይ የተሳተፈ ሲሆን በብራዚልም ጉብኝቶችን አድርጓል።

የልዑኩን ቆይታ አስመልክቶ በብራዚል የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸውም ልዑክ ቡድኑ የብራዚል አፍሪካ የግብርና ዘርፍ ላይ ያተኮረ ጉባኤ ላይ መሳተፉን ተናግረዋል።

ከጉባኤው ጎን ለጎን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከብራዚል ምክትል ፕሬዝዳንት ጋር ግብርናን ጨምሮ በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቱሪዝም እና በአቪዬሽን ዘርፍ ያሉትን ግንኙነት ማሳደግ የሚያስችል ውይይት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

ጉባኤው ብራዚልና አፍሪካ በግብርናው ዘርፍ በጋራ ለመስራት ልምድ በመለዋወጥ ረገድ እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ያተኮረ ስኬታማ መሆኑን ተረናግረዋል።

ከጉባኤው ጎን ለጎን የሀገሪቱን የግብርና ዘርፍ ተግባራት የመስክ ምልከታ መደረጉን ገልጸው፤ በዚህም ልምድ የተወሰደበት መሆኑን አምባሳደሩ አንስተዋል።

በርካታ ተሞክሮዎች የተገኙበት መሆኑን ም ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ ከብራዚል ጋር ያላትን የግብርና ዘርፍ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚያስችል እንደሆነ አስረድተዋል።

በጉባኤው ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ያስመዘገበቻቸውን ስኬቶች ለአፍሪካ ሀገራት እና ለብራዚል ማጋራቷን አምባሳደሩ ገልፀዋል።

በአረንጓዴ ልማት፣ በሌማት ትሩፋት፣ በስንዴ ምርትና ምርታማነት የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማጋራት መቻሉንም ጠቅሰዋል።

በግብርና ዘርፍ ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል የሁለትዮሽ የግብርና ትብብር ስምምነት መፈረሙንም አንስተዋል።

ጉባኤው እና ጉብኝቱ ለሀገራችን ግብርና ዘርፍ ተሞክሮ የተወሰደበት በተለይ ግብርና በቴክኖሎጂ ሲታገዝ የላቀ ለውጥ እንደሚያመጣ መገንዘብ የታቸለበት ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026