
አዲስ አበባ፤ግንቦት 16/2017(ኢዜአ)፦ የብራዚል አፍሪካ የግብርና ዘርፍ ጉባኤ ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ከብራዚል ጋር ያላትን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ያስቻለ መሆኑን በብራዚል የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ገለፁ።
በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስን ጥሩነህ የተመራ ልዑክ በምግብ ዋስትና፣ ረሃብን በመዋጋት እና በገጠር ልማት አጀንዳዎች ላይ ባተኮረው ሁለተኛው የብራዚልና አፍሪካ ጉባኤ ላይ የተሳተፈ ሲሆን በብራዚልም ጉብኝቶችን አድርጓል።
የልዑኩን ቆይታ አስመልክቶ በብራዚል የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸውም ልዑክ ቡድኑ የብራዚል አፍሪካ የግብርና ዘርፍ ላይ ያተኮረ ጉባኤ ላይ መሳተፉን ተናግረዋል።
ከጉባኤው ጎን ለጎን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከብራዚል ምክትል ፕሬዝዳንት ጋር ግብርናን ጨምሮ በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቱሪዝም እና በአቪዬሽን ዘርፍ ያሉትን ግንኙነት ማሳደግ የሚያስችል ውይይት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።
ጉባኤው ብራዚልና አፍሪካ በግብርናው ዘርፍ በጋራ ለመስራት ልምድ በመለዋወጥ ረገድ እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ያተኮረ ስኬታማ መሆኑን ተረናግረዋል።
ከጉባኤው ጎን ለጎን የሀገሪቱን የግብርና ዘርፍ ተግባራት የመስክ ምልከታ መደረጉን ገልጸው፤ በዚህም ልምድ የተወሰደበት መሆኑን አምባሳደሩ አንስተዋል።
በርካታ ተሞክሮዎች የተገኙበት መሆኑን ም ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ ከብራዚል ጋር ያላትን የግብርና ዘርፍ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚያስችል እንደሆነ አስረድተዋል።
በጉባኤው ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ያስመዘገበቻቸውን ስኬቶች ለአፍሪካ ሀገራት እና ለብራዚል ማጋራቷን አምባሳደሩ ገልፀዋል።
በአረንጓዴ ልማት፣ በሌማት ትሩፋት፣ በስንዴ ምርትና ምርታማነት የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማጋራት መቻሉንም ጠቅሰዋል።
በግብርና ዘርፍ ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል የሁለትዮሽ የግብርና ትብብር ስምምነት መፈረሙንም አንስተዋል።
ጉባኤው እና ጉብኝቱ ለሀገራችን ግብርና ዘርፍ ተሞክሮ የተወሰደበት በተለይ ግብርና በቴክኖሎጂ ሲታገዝ የላቀ ለውጥ እንደሚያመጣ መገንዘብ የታቸለበት ነው ብለዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026