የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

May 26, 2025

IDOPRESS

ሮቤ ፤ግንቦት 16/2017(ኢዜአ) ፡-በኦሮሚያ ክልል የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችሉ የግንባታ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸው ተገለጸ።


በብልጽግና ፓርቲ ኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ መንግሥቱ በቀለ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች በሮቤ ከተማ አስተዳደር እየተገነቡ የሚገኙ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።


ኃላፊው መንግሥቱ በቀለ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደተናገሩት፤ የክልሉ መንግሥት የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች የሚመልሱና ተጠቃሚነቱን ለሚያረጋግጡ የግንባታ ፕሮጀክቶች ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።


በተለይ የህዝቡን የመልማት ፍላጎት ታሳቢ ያደረጉና ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናክረው መቀጠላቸውን አመልክተዋል።


በሮቤ ከተማ አስተዳደር እየተገነቡ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶችና ኢኒሼቲቮች የጥረቱ ማሳያዎችና ለብልጽግና ጉዞ ስኬት የላቀ ድርሻ ያላቸው መሆኑን አመልክተዋል።


የሮቤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዲኖ አሚን በበኩላቸው፥አስተዳደሩ ከተማውን ለነዋሪው ምቹ የመኖሪያ ቦታና የቱሪዝምና ንግድ ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው።


አስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ የከተማዋን የንግድ ማዕከልነት ይበልጥ የሚያሳድጉ ከ60 በላይ ፕሮጀክቶች በግንባታ ሂደት ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።


የከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጉብኝትም በዘርፉ የሚታዩ መልካም አጋጣሚዎችና የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች እንዲፈቱ አቅም እንደሚፈጥር አመልክተዋል።


በአመራሮቹ ከተጎበኙ የልማት ፕሮጄክቶች መካከል የ''ሎላ ሻያ'' የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክት፣የንብ ማነብና ዶሮ እርባታ ማዕከል ግንባታን ጨምሮ ሌሎች በከተማ አስተዳደሩ እየተከናወኑ የሚገኙ ኢኒሼቲቮች ተጎብኝቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026