
ሮቤ ፤ግንቦት 16/2017(ኢዜአ) ፡-በኦሮሚያ ክልል የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችሉ የግንባታ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸው ተገለጸ።
በብልጽግና ፓርቲ ኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ መንግሥቱ በቀለ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች በሮቤ ከተማ አስተዳደር እየተገነቡ የሚገኙ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።
ኃላፊው መንግሥቱ በቀለ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደተናገሩት፤ የክልሉ መንግሥት የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች የሚመልሱና ተጠቃሚነቱን ለሚያረጋግጡ የግንባታ ፕሮጀክቶች ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።
በተለይ የህዝቡን የመልማት ፍላጎት ታሳቢ ያደረጉና ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናክረው መቀጠላቸውን አመልክተዋል።
በሮቤ ከተማ አስተዳደር እየተገነቡ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶችና ኢኒሼቲቮች የጥረቱ ማሳያዎችና ለብልጽግና ጉዞ ስኬት የላቀ ድርሻ ያላቸው መሆኑን አመልክተዋል።
የሮቤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዲኖ አሚን በበኩላቸው፥አስተዳደሩ ከተማውን ለነዋሪው ምቹ የመኖሪያ ቦታና የቱሪዝምና ንግድ ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው።
አስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ የከተማዋን የንግድ ማዕከልነት ይበልጥ የሚያሳድጉ ከ60 በላይ ፕሮጀክቶች በግንባታ ሂደት ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።
የከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጉብኝትም በዘርፉ የሚታዩ መልካም አጋጣሚዎችና የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች እንዲፈቱ አቅም እንደሚፈጥር አመልክተዋል።
በአመራሮቹ ከተጎበኙ የልማት ፕሮጄክቶች መካከል የ''ሎላ ሻያ'' የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክት፣የንብ ማነብና ዶሮ እርባታ ማዕከል ግንባታን ጨምሮ ሌሎች በከተማ አስተዳደሩ እየተከናወኑ የሚገኙ ኢኒሼቲቮች ተጎብኝቷል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026