
ሮቤ ፤ግንቦት 16/2017(ኢዜአ) ፡-በኦሮሚያ ክልል የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችሉ የግንባታ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸው ተገለጸ።
በብልጽግና ፓርቲ ኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ መንግሥቱ በቀለ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች በሮቤ ከተማ አስተዳደር እየተገነቡ የሚገኙ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።
ኃላፊው መንግሥቱ በቀለ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደተናገሩት፤ የክልሉ መንግሥት የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች የሚመልሱና ተጠቃሚነቱን ለሚያረጋግጡ የግንባታ ፕሮጀክቶች ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።
በተለይ የህዝቡን የመልማት ፍላጎት ታሳቢ ያደረጉና ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናክረው መቀጠላቸውን አመልክተዋል።
በሮቤ ከተማ አስተዳደር እየተገነቡ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶችና ኢኒሼቲቮች የጥረቱ ማሳያዎችና ለብልጽግና ጉዞ ስኬት የላቀ ድርሻ ያላቸው መሆኑን አመልክተዋል።
የሮቤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዲኖ አሚን በበኩላቸው፥አስተዳደሩ ከተማውን ለነዋሪው ምቹ የመኖሪያ ቦታና የቱሪዝምና ንግድ ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው።
አስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ የከተማዋን የንግድ ማዕከልነት ይበልጥ የሚያሳድጉ ከ60 በላይ ፕሮጀክቶች በግንባታ ሂደት ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።
የከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጉብኝትም በዘርፉ የሚታዩ መልካም አጋጣሚዎችና የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች እንዲፈቱ አቅም እንደሚፈጥር አመልክተዋል።
በአመራሮቹ ከተጎበኙ የልማት ፕሮጄክቶች መካከል የ''ሎላ ሻያ'' የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክት፣የንብ ማነብና ዶሮ እርባታ ማዕከል ግንባታን ጨምሮ ሌሎች በከተማ አስተዳደሩ እየተከናወኑ የሚገኙ ኢኒሼቲቮች ተጎብኝቷል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026