የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የወጪና ገቢ ንግድ እንቅስቃሴን ውጤታማ ለማድረግ የባለ ድርሻ አካላት ሚና የላቀ ነው

May 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 18 /2017(ኢዜአ)፦የሎጂስቲክስ ዘርፉ ቀልጣፋና ተደራሽ በማድረግ የወጪና ገቢ ንግድ እንቅስቃሴን ውጤታማ ለማድረግ የባለ ድርሻ አካላት ሚና የላቀ መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ ከከባድ መኪና አሽከርካሪዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር የጭነት ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ አገልግሎትን የበለጠ ማቀላጠፍ በሚያስችል ጉዳይ ላይ በሞጆ ደረቅ ወደብ የምክክር መድረክ አካሂዷል።


መድረኩ የሎጂስቲክስ ስርዓቱን ቀልጣፋ እና ተደራሽ በማድረግ የገቢና ወጪ ንግድ እንቅስቃሴን ለማሳለጥ የባለድርሻ አካላትን ሚና ለማጎልበት የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታው ዴንጌ ቦሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ወሳኝ ሚና ይጫወታል።

የሎጂስቲክስ ዘርፉን ቀልጣፋና ተደራሽ በማድረግ የወጪና ገቢ ንግድ እንቅስቃሴን ውጤታማ ለማድረግ የባለድርሻ አካላት ሚና የላቀ ነው።

ለዚህም ግንባር ቀደም ሚና የሚጫወቱት የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች መሆናቸው ነው ያነሱት።

የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ምርትንና አገልግሎትን ከቦታ ወደ ቦታ በማጓጓዝ በወቅቱ ለገበያ እንዲቀርብ በማድረግ በኩል ያላቸው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ ብሎም በሌሎች የአለም ሀገራት የሎጂስቲክስ ስርአት መቀላጠፍ የኢኮኖሚ እድገትን ለማፍጠን ትልቁን ድርሻ እንደሚይዝ ሚኒስትር ዴኤታው አክለዋል።

በኢትዮጵያ በተለይም የገቢና ወጪ ጭነት እንቅስቃሴ ውስጥ 86 በመቶ የሚሆነው በከባድ መኪኖች እንደሚጓጓዝ ገልፀዋል።

በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሎጂስቲክስ ዘርፍ አማካሪ መንግስቴ ሃይለማርያም (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አሽከርካሪዎች የትራንስፖርት ዘርፉ ቀልጣፋና አስተማማኝ ብሎም ደህንነቱ የተጠበቀ እንዲሆን ድርሻቸው የላቀ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በተለይም ድንበር ተሻጋሪ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የሎጂስቲክስ ዘርፉን ለማሻሻል በሚደረገው እንቅስቃሴ የራሳቸው ሚና እንዲጫወቱ መሰል መድረኮች መዘጋጀታቸው ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ነው ያነሱት።

በኢትዮጵያ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማህበር አስተባባሪና እና የተሽከርካሪ ባለቤት አቶ ቴድሮስ ሲሳይ በሀገር ኢኮኖሚያዊ እድገት ላይ አሽከርካሪዎች ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ መሰል መድረኮች መዘጋጀታቸው አበረታች ነው ይላሉ።

በዘርፉ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያስችል አቅጣጫ ለማስቀመጥ አይነተኛ ሚና እንዳላቸው ጠቅሰዋል።

እንደዘርፉ ተዋናይም የሎጂስቲክስ ዘርፉን ቀልጣፋና ተደራሽ በማድረግ የወጪና ገቢ ንግድ እንቅስቃሴን ውጤታማ እንዲሆን የድርሻቸውን እንደሚወጡ ነው የተናገሩት።

ሌላኛው የከባድ መኪና አሽከርካሪ አቶ ፀጋዬ ጉታ በበኩላቸው፥ መድረኩ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ያላቸውን ጠንካራ ጎን አጠናክረው እንዲቀጥሉና ክፍተታቸውን እንዲሞሉ የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025