
አዳማ፤ግንቦት19/2017 (ኢዜአ)፦ከእንስሳት ሀብት ልማት የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ የሚያግዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።
ሚኒስቴሩ ከአለም አቀፍ የእንስሳት ምርምር ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን ''የኢትዮጵያ እንስሳትና ዓሳ ሀብት ኢንቨስትመንት ሰነድ''ለክልልና በየደረጃው ለሚገኙ ባለድርሻ አካላት ለማስተዋወቅ ያዘጋጀው መድረክ በአዳማ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ ላይ የግብርና ኢንቨስትመንትና ግብዓት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሶፍያ ካሳ (ዶ/ር) እንዳሉት፥ በአገራችን ካለው ሰፊ የእንስሳት ሃብት አኳያ በዘርፉ በሚፈለገው መጠን ጥቅም እየተገኘ አይደለም።
ሀገሪቷ ካላት አቅም አንፃር ወደ ውጪ ከሚላከው የእንስሳት ተዋፅኦ እየተገኘ ያለው 130 ሚሊዮን ዶላር አመታዊ ገቢ መሆኑን ጠቅሰው፥ ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ ቅንጅታዊ አሰራርን ማጎልበት እንደሚጠይቅ አመልክተዋል።
በኢትዮጵያ የአለም አቀፉን መስፈርትና ደረጃን ያሟሉ 10 ቄራዎች ቢኖሩም በእንስሳት አቅርቦት ችግር ሳቢያ የሚጠበቀውን ያህል እየሰሩ አለመሆኑን ተናግረዋል።
በመሆኑም ሀገሪቷ ያላትን ሀብት ወደ ቄራዎቹ በማምጣት የተሻለ ጥቅምና የውጭ ምንዛሪ ግኝታችንን ይበልጥ ማስፋፋት ያስፈልጋል ብለዋል።
የሌማት ትሩፋት ከተጀመረ ወዲህ መነቃቃት እና ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እየተገኘ ቢሆንም በእንስሳት ዘርፉ ከቦታ ልየታ አንስቶ የቴክኒክ ድጋፍ ውስንነቶች እንዳሉ አመላክተዋል።
የግሉ ባለሀብትም በዘርፉ ለመሰማራት ያሳየው ቁርጠኝነት አነስተኛ በመሆኑ ተሳትፎውን ሊያሳድግ እንደሚገባ ጠቁመው፥ ወጣቶችንም በዘርፉ በስፋት በማሳተፍ ለስራ እድልና ለውጭ ምንዛሪ ግኝት መጠናከር በቅንጅት መስራት ይገባል ብለዋል።
በዚህ ረገድም ሚኒስቴሩ የእንስሳት ሃብት ልማቱን ለማስፋፋትና ለማዘመን የሚያስችል ሰነድ ማዘጋጀቱን ጠቅሰው፥ ሰነዱ ሀገሪቷ በእንስሳት ዘርፍ ያላትን አማራጮች ያመላከተ መሆኑን ገልፀዋል።
በመሆኑም ሁሉም ክልሎች ካላቸው ነባራዊ ሁኔታ አንፃር በመቃኘት ስራ ላይ ማዋል እንደሚገባቸውም አሳስበዋል።
በግብርና ሚኒስቴር የእንስሳትና ዓሳ ልማት ዘርፍ አማካሪ አቶ ግርማ ሙሉጌታ በበኩላቸው፥ የእንስሳት እርባታ ዘርፍ ለስራ እድል ፈጠራ፣ የውጭ ምንዛሬ ገቢን ለማሳደግ፣ ለኢንዱስትሪ ጥሬ እቃነት ለማዋል በሚያስችል መልኩ እየተሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
የተዘጋጀው ሰነድም የኢንቨስትመንቱን እንቅስቃሴ በማነቃቃትና ኢትዮጵያን ከልማቱ ተጠቃሚ ለማድረግ ድልድይ ሆኖ ያገለግላል ብለዋል።
በቀጣይም የእንስሳትና ዓሳ ንዑስ ዘርፎችን ወደ ዘመናዊ፣ተወዳዳሪ እና ለኤክስፖርት ብዝሃነት ቀጣይነት አይነተኛ መሳሪያነት ለመጠቀም ሁሉም ሊረባረብ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026