የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማትና በኮንስትራክሽን በርካታ የሥራ ዕድል እየፈጠረች ነው

May 28, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 19/2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማትና በኮንስትራክሽን ዘርፍ በርካታ የሥራ ዕድል እየፈጠረች መሆኗ የሚደነቅ ነው ሲሉ የዓለም ሥራ ድርጅት የሥራ፣ ልማትና ኢንቨስትመንት ክፍል ሃላፊ ሚቶ ትሱካሞቶ ገለጹ፡፡


ኢትዮጵያ 20ኛውን የዓለም ሥራ ድርጅት ቀጣናዊ ስብሰባ በብቃት በማስተናገድ በታዳሚዎች ዘንድ እውቅና ተችሯታል፡፡


በአዲስ አበባ የተገነቡ የአረንጓዴ ልማት፣የቱሪዝም ስፍራዎች፣ ኢንዱስትሪ ፓርኮችና የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶችን በመጎብኘት ኢትዮጵያ የሥራ ዕድል ፈጠራና ዘላቂ ልማት ትኩረት መስጠቷን አረጋግጠዋል፡፡


የዓለም ሥራ ድርጅት የሥራ፣ ልማትና ኢንቨስትመንት ክፍል ሃላፊ ሚቶ ትሱካሞቶ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በአዲስ አበባ የተጀመረው የኮንስትራክሽን ዘርፍ በርካታ የሥራ እድል መፍጠሩን የሚደነቅ ነው፡፡


ወደ አዲስ አበባ የመጣሁት ከስምንት ዓመት በፊት ኢትዮጵያ 17ኛው የዓለም የሥራ ድርጅት አህጉራዊ ስብሰባ ስታስተናግድ ነበር ያሉት ሃላፊዋ፤ አሁን አስደናቂ ለውጦችን መመልከታቸውን ገልጸዋል፡፡


በአዲስ አበባ በርካታ የተገነቡና በመገንባት ላይ ያሉ ፕሮጀክቶች መኖራቸውን ገልጸው፤ የኮንስትራክሽን ስራዎች ኢንቨስትመንትን በመሳብ ሰፊ የሥራ ዕድል እየፈጠሩ ነው ብለዋል፡፡


የመሰረተ ልማት ዝርጋት ከፍተኛ የሆነ የሥራ ዕድል የመፍጠር አቅም እንዳለው የገለጹት ሃላፊዋ፥ኢትዮጵያ አረንጓዴ ከተሞችን የመገንባት ሂደት ላይ መሆኗን ተረድቻለሁ ብለዋል፡፡


ኢትዮጵያ የዓለም ሥራ ድርጅት የሥራ ዕድል በሚፈጥሩ የመሰረተ ልማት ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ ሀገራት የሚያደርገው ድጋፍ ተጠቃሚ እንደሆነች ገልጸዋል፡፡


የኮንስትራክሽን ሥራዎች የአካበባው ማህበረሰብ በባለቤትነት እንዲሳተፍበት የሚያደርግ መሆኑን በማንሳት፤ በኢትዮጵያ በተለይም በአዲስ አበባ የተመለከትኩት ይሄን ነው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025