
አዲስ አበባ፤ግንቦት 19/2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማትና በኮንስትራክሽን ዘርፍ በርካታ የሥራ ዕድል እየፈጠረች መሆኗ የሚደነቅ ነው ሲሉ የዓለም ሥራ ድርጅት የሥራ፣ ልማትና ኢንቨስትመንት ክፍል ሃላፊ ሚቶ ትሱካሞቶ ገለጹ፡፡
ኢትዮጵያ 20ኛውን የዓለም ሥራ ድርጅት ቀጣናዊ ስብሰባ በብቃት በማስተናገድ በታዳሚዎች ዘንድ እውቅና ተችሯታል፡፡
በአዲስ አበባ የተገነቡ የአረንጓዴ ልማት፣የቱሪዝም ስፍራዎች፣ ኢንዱስትሪ ፓርኮችና የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶችን በመጎብኘት ኢትዮጵያ የሥራ ዕድል ፈጠራና ዘላቂ ልማት ትኩረት መስጠቷን አረጋግጠዋል፡፡
የዓለም ሥራ ድርጅት የሥራ፣ ልማትና ኢንቨስትመንት ክፍል ሃላፊ ሚቶ ትሱካሞቶ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በአዲስ አበባ የተጀመረው የኮንስትራክሽን ዘርፍ በርካታ የሥራ እድል መፍጠሩን የሚደነቅ ነው፡፡
ወደ አዲስ አበባ የመጣሁት ከስምንት ዓመት በፊት ኢትዮጵያ 17ኛው የዓለም የሥራ ድርጅት አህጉራዊ ስብሰባ ስታስተናግድ ነበር ያሉት ሃላፊዋ፤ አሁን አስደናቂ ለውጦችን መመልከታቸውን ገልጸዋል፡፡
በአዲስ አበባ በርካታ የተገነቡና በመገንባት ላይ ያሉ ፕሮጀክቶች መኖራቸውን ገልጸው፤ የኮንስትራክሽን ስራዎች ኢንቨስትመንትን በመሳብ ሰፊ የሥራ ዕድል እየፈጠሩ ነው ብለዋል፡፡
የመሰረተ ልማት ዝርጋት ከፍተኛ የሆነ የሥራ ዕድል የመፍጠር አቅም እንዳለው የገለጹት ሃላፊዋ፥ኢትዮጵያ አረንጓዴ ከተሞችን የመገንባት ሂደት ላይ መሆኗን ተረድቻለሁ ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ የዓለም ሥራ ድርጅት የሥራ ዕድል በሚፈጥሩ የመሰረተ ልማት ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ ሀገራት የሚያደርገው ድጋፍ ተጠቃሚ እንደሆነች ገልጸዋል፡፡
የኮንስትራክሽን ሥራዎች የአካበባው ማህበረሰብ በባለቤትነት እንዲሳተፍበት የሚያደርግ መሆኑን በማንሳት፤ በኢትዮጵያ በተለይም በአዲስ አበባ የተመለከትኩት ይሄን ነው ብለዋል፡፡
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026