የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ ያለው ሰፊ የዓሳ ሀብት በቴክኖሎጂ ታግዞ በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውል የተጀመረው ድጋፍ ይጠናከራል -ሚኒስቴሩ

May 30, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ግንቦት 21/2017(ኢዜአ)፡-በጋምቤላ ክልል ያለው ሰፊ የዓሳ ሀብት በቴክኖሎጂ ታግዞ በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውል የተጀመረው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ።


የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) በጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጽህፈት ቤት የተገነባውን ዘመናዊ ዲጂታል ስማርት የኮሙኒኬሽን ማሳለጫ ክፍል ስራ በማስጀመር በክልሉ ዓሳ ሀብት ልማት ዙሪያ ከክልሉ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።


በዚህ ወቅት ሚኒስትር ዴኤታው፥በክልሉ ያለው እምቅ የዓሳ ሀብት በቴክኖሎጂ ታግዞ የሚፈለገውን ጥቅም እንዲያስገኝ እየተደረገ ያለው ጥረት አበረታች መሆኑን ተናግረዋል።


ለዚህ መሳካት የሚኒስቴሩ ድጋፍ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።


ሚኒስቴሩ ቀደም ሲል በክልሉ የዓሳ ሀብት ልማቱን ለማዘመን የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ሶስት የዓሳ ማቀነባበሪያና የግብይት ማዕከላት ግንባታን ጨምሮ የዓሳ ማጥመጃና ማቆያ የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን ድጋፍ ማድረጉን አስታውሰዋል።


በቀጣይም የዘርፉን ልማት በማዘመን ሀብቱ ለክልሉ ብሎም ለሀገር የኢኮኖሚ ግንባታ እንዲውል እየተደረገ ላለው ጥረት ሚኒስቴሩ የጀመራቸውን ሁለንተናዊ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።


የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን ከመደገፍ ባለፈም በዘርፉ ለተሰማሩ ወጣቶች የገበያ ትስስር እንዲፈጠርላቸው ጭምር እገዛ እንደሚደረግም ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል።


የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ በክልሉ ሰፊ የዓሳ ሀብት ቢኖርም በዘመናዊ መልኩ በማልማትና ጥቅም ላይ በማዋል ረገድ ውስንነቶች መኖራቸውን አንስተዋል።


የዓሳ ሀብቱን ዘመናዊ የገበያ ሰንሰለት በመጠቀም ወደ ገበያ የማቅረቡ ስራ እንዳለ ሆኖ በቋንጣ መልክ እየተዘጋጀ ለገበያ እየቀረበ እንደሚገኝም ገልጸዋል።


በመሆኑም በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተጀመሩት የቴክኖሎጂ ድጋፍና እገዛዎች እንዲጠናከሩ ምክትል ርዕሰ መስተዳደሩ ጠይቀዋል።


በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እየተደረጉ ካሉት የቴክኖሎጂ ግብዓት ድጋፎች በተጨማሪ የቴክኒክ እገዛ ጭምር ያስፈልጋል ያሉት ደግሞ የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፖል ጋሪ ናቸው።


በጋምቤላ ክልል በዓመት እስከ 20 ሺህ ቶን ዓሳ ማምረት የሚያስችል አቅም እንዳለ ከክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሀብት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025