የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ጉባኤው አህጉራዊ የመድኅን አገልግሎትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ልምዶች የተቀሰሙበት ነው-አቶ ያሬድ ሞላ

May 30, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 20/2017(ኢዜአ)፦የአፍሪካ ኢንሹራንስ ድርጅት ጉባኤ አህጉራዊ የመድኅን አገልግሎት የሚያስችሉ ልምዶች የተቀሰሙበት መሆኑን የድርጅቱ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የኢትዮጵያ መድኅን ሰጪዎች ፕሬዝዳንት አቶ ያሬድ ሞላ ገለጹ።


''የክፍያ ሚዛንን ማስተካከል፥ የአፍሪካ የእዳ ጫና፣ የሃገራት እዳ የኢንሹራንስ ድርጅቶች ላይ ምን ተጽዕኖ ያሳድራል?" በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው የአፍሪካ ኢንሹራንስ ድርጅት ዓመታዊ ጉባኤ ተጠናቋል።


የድርጅቱ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የኢትዮጵያ መድኅን ሰጪዎች ፕሬዝዳንት አቶ ያሬድ ሞላ፥ጉባኤው በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ምክክር በማድረግ መግባባት የተፈጠረበት መሆኑን ገልጸዋል።


ከአፍሪካና ከሌሎች የዓለም ክፍል 93 ሀገራትን የወከሉ ከ1 ሺህ 900 በላይ ተሳታፊዎች በጉባኤው መገኘታቸውን ገልጸው፥ ይህም በድርጅቱ የጉባኤ ታሪክ ከፍተኛው ነው ብለዋል።


ኢትዮጵያ ጉባኤውን በስኬት ማስተናገዷ ተሳታፊ ልዑካን ቡድኖችን ያስደመመ ክስተትና ለኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት ምስጋና የቀረበበት መሆኑን ተናግረዋል።


የሀገራትን የዕዳ ጫና በሚመለከት የቀረቡ ጥናታዊ ጽሁፎች ለሕግ አውጪዎችና ኢንሹራንስ አስተዳዳሪዎች በማሰራጨት ለፖሊሲ ግብዓትነት ማዋል የሚያስችል ምክክር መደረጉን ገልጸዋል።


ከመድኅን አገልግሎት ዕድገት፣ስርጸትና የነፍስ ወከፍ መጠን መለኪያ አንፃር ብዙ ስራዎች ይጠብቁናል ነው ያሉት።


በጉባኤውም ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካን የመድኅን አገልግሎት ለማሳደግ የሚያስችሉ ልምድና ተሞክሮዎች ጠንካራ የመድህን ስርዓትና አገልግሎት ከገነቡ ሀገራት መቀሰማቸውን አንስተዋል።


የአፍሪካ መድኅን ድርጅት ፕሬዝዳንት ፓቲ ማርቲን፥የጋራ ትብብርን በማጠናከር የአፍሪካን መድኅን ኢንዱስትሪ ለማሳደግ ገንቢ ምክክር ተደርጓል ብለዋል።


የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ጉባኤው በስኬት እንዲጠናቀቅ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል።


የኢትዮጵያ ጠለፋ መድኅን አክሲዮን ማኅበር ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚና የመድኅን ባለሙያዎች ማኅበር ምክትል ፕሬዝዳንት ፍቅሩ ጸጋዬ፥በኢትዮጵያ ሀገር በቀል የመረዳጃ ማህበራትን ጨምሮ እድሜ ጠገብና ዘመናዊ የመድኅን ሰጪ ተቋማት መኖራቸውን ገልጸዋል።


በመላ ሀገሪቱ የህይወት፣ ንብረትና የሕጋዊ ኃላፊነት መድኅን አገልግሎት የሚሰጡ 18 የመድኅን አገልግሎት ሰጪ ኩባንያዎች እንዳሉ ተናግረዋል።


በጉባኤው የቀረቡ የመነሻ ጽሁፍ ምክረ ሃሳቦችን ለኢትዮጵያ መድኅን አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዕድገት ጥቅም ላይ እንዲውሉ ይደረጋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026