የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ጉባኤው አህጉራዊ የመድኅን አገልግሎትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ልምዶች የተቀሰሙበት ነው-አቶ ያሬድ ሞላ

May 30, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 20/2017(ኢዜአ)፦የአፍሪካ ኢንሹራንስ ድርጅት ጉባኤ አህጉራዊ የመድኅን አገልግሎት የሚያስችሉ ልምዶች የተቀሰሙበት መሆኑን የድርጅቱ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የኢትዮጵያ መድኅን ሰጪዎች ፕሬዝዳንት አቶ ያሬድ ሞላ ገለጹ።


''የክፍያ ሚዛንን ማስተካከል፥ የአፍሪካ የእዳ ጫና፣ የሃገራት እዳ የኢንሹራንስ ድርጅቶች ላይ ምን ተጽዕኖ ያሳድራል?" በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው የአፍሪካ ኢንሹራንስ ድርጅት ዓመታዊ ጉባኤ ተጠናቋል።


የድርጅቱ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የኢትዮጵያ መድኅን ሰጪዎች ፕሬዝዳንት አቶ ያሬድ ሞላ፥ጉባኤው በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ምክክር በማድረግ መግባባት የተፈጠረበት መሆኑን ገልጸዋል።


ከአፍሪካና ከሌሎች የዓለም ክፍል 93 ሀገራትን የወከሉ ከ1 ሺህ 900 በላይ ተሳታፊዎች በጉባኤው መገኘታቸውን ገልጸው፥ ይህም በድርጅቱ የጉባኤ ታሪክ ከፍተኛው ነው ብለዋል።


ኢትዮጵያ ጉባኤውን በስኬት ማስተናገዷ ተሳታፊ ልዑካን ቡድኖችን ያስደመመ ክስተትና ለኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት ምስጋና የቀረበበት መሆኑን ተናግረዋል።


የሀገራትን የዕዳ ጫና በሚመለከት የቀረቡ ጥናታዊ ጽሁፎች ለሕግ አውጪዎችና ኢንሹራንስ አስተዳዳሪዎች በማሰራጨት ለፖሊሲ ግብዓትነት ማዋል የሚያስችል ምክክር መደረጉን ገልጸዋል።


ከመድኅን አገልግሎት ዕድገት፣ስርጸትና የነፍስ ወከፍ መጠን መለኪያ አንፃር ብዙ ስራዎች ይጠብቁናል ነው ያሉት።


በጉባኤውም ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካን የመድኅን አገልግሎት ለማሳደግ የሚያስችሉ ልምድና ተሞክሮዎች ጠንካራ የመድህን ስርዓትና አገልግሎት ከገነቡ ሀገራት መቀሰማቸውን አንስተዋል።


የአፍሪካ መድኅን ድርጅት ፕሬዝዳንት ፓቲ ማርቲን፥የጋራ ትብብርን በማጠናከር የአፍሪካን መድኅን ኢንዱስትሪ ለማሳደግ ገንቢ ምክክር ተደርጓል ብለዋል።


የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ጉባኤው በስኬት እንዲጠናቀቅ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል።


የኢትዮጵያ ጠለፋ መድኅን አክሲዮን ማኅበር ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚና የመድኅን ባለሙያዎች ማኅበር ምክትል ፕሬዝዳንት ፍቅሩ ጸጋዬ፥በኢትዮጵያ ሀገር በቀል የመረዳጃ ማህበራትን ጨምሮ እድሜ ጠገብና ዘመናዊ የመድኅን ሰጪ ተቋማት መኖራቸውን ገልጸዋል።


በመላ ሀገሪቱ የህይወት፣ ንብረትና የሕጋዊ ኃላፊነት መድኅን አገልግሎት የሚሰጡ 18 የመድኅን አገልግሎት ሰጪ ኩባንያዎች እንዳሉ ተናግረዋል።


በጉባኤው የቀረቡ የመነሻ ጽሁፍ ምክረ ሃሳቦችን ለኢትዮጵያ መድኅን አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዕድገት ጥቅም ላይ እንዲውሉ ይደረጋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026