
ሚዛን አማን፤ግንቦት 21/2017 (ኢዜአ)፦የቁንዶ በርበሬ ቅመምን በማምረት ከምርት ሽያጩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መሆኑን በሸካ ዞን የየኪ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ።
የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል መነሻ ዘር ከውጭ በማምጣት ያላመደው የቁንዶ በርበሬ ቅመም ምርታማና ለአካባቢው አየር ጸባይ ተስማሚ መሆኑንም አርሶ አደሮቹ ገልጸዋል።
አስተያየታቸውን ከሰጡ አርሶ አደሮች መካከል በየኪ ወረዳ የፊዴ ቀበሌ ነዋሪ ዓይናቸው ካሳሁን፥ በ2 ነጥብ 5 ሄክታር ማሳ ላይ የሚያመርተውን ቁንዶ በርበሬ ለገበያ በማቅረብ ገቢውን እያሳደገ መሆኑን ለኢዜአ ተናግሯል።
ከቁንዶ በርበሬ ማሳው በዓመት እስከ 20 ኩንታል ምርት እንደሚያገኝ ገልጾ፥ዘንድሮ ካለው ምቹ የአየር ሁኔታ በመነሳት የተሻለ ምርት እንደሚጠብቅ አመልክቷል።
በቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል ድጋፍና ክትትል ለተሻለ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት መድረሱን የገለጸው ወጣቱ አርሶ አደር በቀጣይም ልማቱን ለማስፋፋት ግማሽ ሄክታር ማሳ ማዘጋጀቱን ጠቁሟል።
ሌላው የአሮጌ ብርሃን ቀበሌ ነዋሪ አየነው አለልኝ፥ የቁንዶ በርበሬ ልማት ሥራ ባከናወነባቸው ሦስት ዓመታት ውስጥ ከልማቱ በተጨማሪ ችግኝ በማዘጋጀት ለሌሎች አርሶ አደሮች በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን እያሳደገ መሆኑን ተናግሯል።
ካለው አንድ ሄክታር የቁንዶ በርበሬ ማሳ እስከ 10 ኩንታል ምርት እንደሚጠብቅም ገልጿል።
የቁንዶ በርበሬ ዋጋ ከሁለት ዓመታት በፊት ከነበረው በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመምጣቱ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ተናግሯል።
በቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል መነሻ ቴክኖሎጂ ብዜትና ዘር ምርምር የሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ በኃይሉ መኮንን፥ ማዕከሉ የግብርና ቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለአርሶ አደሮች እያቀረበ መሆኑን ተናግረዋል።
ከዚህ በተጨማሪ አዳዲስ የቅመማ ቅመም ዘር ከማዕከሉ የሚወስዱ አርሶ አደሮችን የሥራ እንቅስቃሴ በቅርበት በመከታተልና በመደገፍ ለውጤት ለማብቃት እንደሚሰራ ገልጸዋል።
በዚህም የተሻለ የቅመማ ቅመም ማሳ በአርሶ አደሮች ጓሮ እየታየ መሆኑን ጠቅሰው፥ማዕከሉ መሰል ተግባሩን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የቴፒ ብሔራዊ የቅመማ ቅመም አስተባባሪና ተመራማሪ አቡኪያ ጌቱ፥ የቁንዶ በርበሬ ምርት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እና በጋምቤላ ክልሎች በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች እየተስፋፋ መሆኑን አመልክተዋል።
የቁንዶ በርበሬ ልማት ከዛፎች ጋር ትስስር ስላለው ተፈጥሮን የመጠበቅ ጠባይ አለው ያሉት ተመራማሪው፥ከአንድ ሄክታር የቁንዶ በርበሬ ማሳ ከሚሰበሰብ ምርት ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በመሆኑም አርሶ አደሩን ከልማቱ ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026