የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የቱሪዝም ሚኒስቴር ለ11 ሆቴሎች ባለ አምስት ኮከብ ደረጃ መስጠቱን አስታወቀ

May 30, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 21/2017(ኢዜአ)፦የቱሪዝም ሚኒስቴር መስፈርቱን ላሟሉ 11 ሆቴሎች ባለ አምስት ኮከብ ደረጃ መስጠቱን አስታወቀ።


ሚኒስቴሩ በ2017 በጀት ዓመት በአዲስ አበባ የሚገኙ ነባር እና አዳዲስ ሆቴሎችን ዳግሞ ምዝና በማድረግ አስገዳጅ መስፈርቶችን ላሟሉ ሆቴሎች የኮከብ ደረጃ መስጠቱን ይፋ አድርጓል።


በሚኒስቴሩ የቱሪስት አገልግሎቶች ብቃት ማረጋገጥና ደረጃ ምደባ መሪ ስራ አስፈጻሚ ታሪኩ ደምሴ፥ ደረጃ ከተሰጣቸው ሆቴሎች ውስጥ 34ቱ በዳግም ምዘና ስድስቱ ደግሞ አዲስ አገልግሎት የጀመሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።


የምዘና መስፈርቶች የሆቴል ውጫዊ ገጽታ፣ማብሰያ፣የሆቴሉ ጠቅላላ አገልግሎት፣ጥበቃና ደህንነትን ጨምሮ 12 ዋና ዋና ነጥቦችን ያካተተ ነው ብለዋል።


ስካይላይትና ሸራተን አዲስ ሆቴልን ጨምሮ 11 ሆቴሎች ባለ 5 ኮከብ ደረጃ፣ 9 ሆቴሎች ባለ 4 ኮከብ እንዲሁም 7 ሆቴሎች ባለ 3 ኮከብ፣ አምስት ሆቴሎች ባለ2 እንዲሁም ሁለት ሆቴሎች ባለ አንድ ኮከብ ደረጃ ማግኘታቸውን ተናግረዋል።


አዲስ የተመዘኑ ስድስት ሆቴሎች ከባለ አራት እስከ ባለ ሁለት ኮከብ ደረጃ እንደተሰጣቸው ገልጸዋል።


የተሰጠው ደረጃ በአዲስ አበባ እያደገ የመጣውን የኮንፈረንስ ቱሪዝም የሚመጥን አገልግሎት በመስጠት ከቱሪዝም ዘርፍ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ ጉልህ ድርሻ አለው ተብሏል።


በሆቴሎች መካከል ጤናማ ውድድር እንዲኖርና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግም ያግዛል ብለዋል።


የኮከብ ደረጃው ለ3 ዓመት የሚያገለግል ሲሆን በሚደረገው ክትትልና ቁጥጥር ከደረጃ በታች የወረደ ሆቴል በማንኛውም ጊዜ ደረጃውን ሊነጠቅ እንደሚችል አስገንዝበዋል።


በኢትዮጵያ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማልማት ዘርፉ ለምጣኔ ሃብት እድገት ያለውን ድርሻ ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025