አዲስ አበባ፤ግንቦት 21/2017(ኢዜአ)፦የቱሪዝም ሚኒስቴር መስፈርቱን ላሟሉ 11 ሆቴሎች ባለ አምስት ኮከብ ደረጃ መስጠቱን አስታወቀ።
ሚኒስቴሩ በ2017 በጀት ዓመት በአዲስ አበባ የሚገኙ ነባር እና አዳዲስ ሆቴሎችን ዳግሞ ምዝና በማድረግ አስገዳጅ መስፈርቶችን ላሟሉ ሆቴሎች የኮከብ ደረጃ መስጠቱን ይፋ አድርጓል።
በሚኒስቴሩ የቱሪስት አገልግሎቶች ብቃት ማረጋገጥና ደረጃ ምደባ መሪ ስራ አስፈጻሚ ታሪኩ ደምሴ፥ ደረጃ ከተሰጣቸው ሆቴሎች ውስጥ 34ቱ በዳግም ምዘና ስድስቱ ደግሞ አዲስ አገልግሎት የጀመሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የምዘና መስፈርቶች የሆቴል ውጫዊ ገጽታ፣ማብሰያ፣የሆቴሉ ጠቅላላ አገልግሎት፣ጥበቃና ደህንነትን ጨምሮ 12 ዋና ዋና ነጥቦችን ያካተተ ነው ብለዋል።
ስካይላይትና ሸራተን አዲስ ሆቴልን ጨምሮ 11 ሆቴሎች ባለ 5 ኮከብ ደረጃ፣ 9 ሆቴሎች ባለ 4 ኮከብ እንዲሁም 7 ሆቴሎች ባለ 3 ኮከብ፣ አምስት ሆቴሎች ባለ2 እንዲሁም ሁለት ሆቴሎች ባለ አንድ ኮከብ ደረጃ ማግኘታቸውን ተናግረዋል።
አዲስ የተመዘኑ ስድስት ሆቴሎች ከባለ አራት እስከ ባለ ሁለት ኮከብ ደረጃ እንደተሰጣቸው ገልጸዋል።
የተሰጠው ደረጃ በአዲስ አበባ እያደገ የመጣውን የኮንፈረንስ ቱሪዝም የሚመጥን አገልግሎት በመስጠት ከቱሪዝም ዘርፍ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ ጉልህ ድርሻ አለው ተብሏል።
በሆቴሎች መካከል ጤናማ ውድድር እንዲኖርና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግም ያግዛል ብለዋል።
የኮከብ ደረጃው ለ3 ዓመት የሚያገለግል ሲሆን በሚደረገው ክትትልና ቁጥጥር ከደረጃ በታች የወረደ ሆቴል በማንኛውም ጊዜ ደረጃውን ሊነጠቅ እንደሚችል አስገንዝበዋል።
በኢትዮጵያ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማልማት ዘርፉ ለምጣኔ ሃብት እድገት ያለውን ድርሻ ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025