የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

አርሶ አደሮች በቆሎን በኩታገጠም በማልማት ለገበያ ለማቅረብ እየሰሩ ነው

May 30, 2025

IDOPRESS

ነቀምቴ ፤ ግንቦት 21/2017 (ኢዜአ)፤-በመኽር ወቅቱ በቆሎን በኩታ ገጠም በማልማት ለገበያ ለማቅረብ እየሰሩ መሆናቸውን በምስራቅ ወለጋ ዞን የጉቶ ጊዳ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ።

በምሰራቅ ወለጋ ዞን በዘንድሮ መኽር ወቅት 80ሺህ 820 ሄክታር ኩታገጠም ማሳ ላይ በቆሎ እንደሚለማ የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታውቋል ።


በዞኑ በመኽር ወቅቱ ቀድመው ከሚዘሩ ሰብሎች አንዱ በቆሎ ሲሆን በዞኑ የጉቶ ጊዳ ወረዳ የኩታ ገጠም በቆሎ ልማት የዘር ስራ ዛሬ ተጀምሯል።

የወረዳው ነዋሪ አርሶ አደር አስፍው ለማ እንደተናገሩት የአካባቢው አርሶ አደሮች 1ሺ 33 ሄክታር መሬት ላይ በቆሎን በኩታገጠም በማልማት ለገበያ ለማቅረብ ዘር መዝራት ጀምረዋል ።

በቆሎን በተሻለ ጥራትና ብዛት በስፋት ለማልማት አቅደው ወደ ስራ መግባታቸውን ጠቁመው በግብርና ፅህፈት ቤት በኩል አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ተናግረዋል።

ሌላው የወረዳው ነዋሪ አርሶ አደር ወርቅነህ ገለታ በበኩላቸው ሰብልን በተናጠል ማልማት ውጤቱ እንብዛም መሆኑን ጠቁመው በኩታገጠም ማልማት አቅምን በማጎልበት የተሻለ ምርት እንደሚያስገኝ ተናግረዋል ።


አርሶ አደሮች በኩታ ገጠም በመደራጀት አንድ ሺ ሄክታር መሬት ላይ በቆሎ በማልማት ከ80ሺ ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት አቅደው የዘር ስራ መጀመራቸውን አመልክተዋል ።

የምስራቅ ወለጋ ዞን ግብርና ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አስፍው ሀንቢሳ በዞኑ በዘንድሮ መኽር ወቅት ከ80ሺ 820 ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም በበቆሎ ዘር የመሸፈን ስራ መጀመሩን ተናግረዋል።

ለልማቱ የሚያገለግል 22ሺ ኩንታል የበቆሎ ምርጥ ዘር ቀርቦ እስካሁን ከ19ሺ ኩንታል በላዩ መከፍፈሉን ተናግረዋል ።


የማዳበሪያ አቅርቦትና ስርጭትም እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል ።

የሰብሉን ምርታማነት ለማሳደግ የእርሻ ስራውን የማዘመንና ለኩታገጠም አስተራረስ ዘዴ ትኩረት መሰጠቱን አስታውቀዋል ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026