አዲስ አበባ፤ ግንቦት 26/2017(ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አራተኛውን እና የክረምት በጎ ፍቃድ ስራ አካል የሆነውን የገጠር ኮሪደር ልማት ስራ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ሁልባረግ ወረዳ ወራበት ሻማ ቀበሌ ሞዴል የአርሶ አደሮች የመኖሪያ መንደር ግንባታ አስጀምረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት አራተኛውን እና የክረምት በጎ ፍቃድ ስራ አካል የሆነውን የገጠር ኮሪደር ልማት ስራ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ሁልባረግ ወረዳ ወራበት ሻማ ቀበሌ ሞዴል የአርሶ አደሮች የመኖሪያ መንደር ግንባታ አስጀምረናል ብለዋል።
እነዚህ መኖሪያዎች ተገንብተው ሲጠናቀቁ የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘዬ የሚቀይሩ እና ጤናማ ህይወትን የሚያላብሱት ናቸው ሲሉም ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በዞኑ በነበረን ቆይታ የግሉ ዘርፍ በአግሮ ኢንደስትሪ ላይ ያለውን ተሳትፎ ተመልክተናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
እንደማሳያ አቶት የተቀናጀ አግሮ ኢንደስትሪን ተዘዋውረን ተመልክተናል ነው ያሉት።
እንዲህ ያሉት ስራዎች በሌማት ትሩፋት ውጤት ለማስመዝገብ የተጀመረውን ተግባር ከግብ ለማድረስ በጎ ጅምሮች በመሆናቸው ሊበረታቱ ይገባል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025