ጋምቤላ፤ግንቦት 27/2017 (ኢዜአ)፦የኮሪደር ልማቱን በማፋጠን ከተማዋን ለነዋሪዎቿና ለቱሪዝም ምቹ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የጋምቤላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ገለጹ።
በከተማዋ በአራቱም አቅጣጫ የ14 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ ለማከናወን ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን የጋምቤላ ከተማ ከንቲባ ሳይመን ሙን (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ከንቲባ ሳይመን ሙን (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የተጀመረውን የኮሪደርና የውስጥ ለውስጥ የመንገድ መሰረተ ልማት በማፋጠን ከተማዋን ለነዋሪዎቿና ለቱሪስት መዳረሻነት ምቹ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው።
የጋምቤላ ከተማ ብዙ ዓመታትን ያስቆጠረችና የንግድ ቀጠና የነበረች ታሪካዊ ከተማ ብትሆንም የእድሜዋን ያህል ያላደገችና የመንገድ መሰረተ ልማት ችግር ያለባት ከተማ መሆኗንም አስታውሰዋል።
ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የከተሞች ልማት ስትራቴጂ ፖሊሲን ታሳቢ በማድረግ መንገድና ሌሎች የመሰረተ ልማት አውታሮችን ለማሟላት ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይ የከተሞች የኮሪደር ልማትን በማጠናከር ከተማዋን ውብ፣ጽዱና ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በከተማዋ በመጀመሪያው ዙር በተለያዩ አቅጣጫዎች የ14 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ በአራት ምዕራፍ ተከፋፍሎ ለመገንባት ግብ ተይዞ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።
በከተማው እየተከናወነ ባለው የኮሪደር ልማት የሥራ ዕድል ካገኙ ዜጎች መካከል ወጣት ሳዳም አብዱ በሰጠው አስተያየት፥ የኮሪደር ልማት ለከተማው እድገት ከሚኖረው ፋይዳ ባለፈ የሥራ እድል ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን ተናግሯል።
ኮሪደር ልማት የአካባቢን ገጽታ ለመቀየርና ስራ አጥ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መርሃ ግብር መሆኑን የገለጸው ደግሞ ሌላው በከተማው ኮሪደር ልማት እየተሳተፈ ያለው ወጣት ኑርሴን አብዱልቃደር ነው።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025