
ጋምቤላ፤ግንቦት 27/2017 (ኢዜአ)፦የኮሪደር ልማቱን በማፋጠን ከተማዋን ለነዋሪዎቿና ለቱሪዝም ምቹ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የጋምቤላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ገለጹ።
በከተማዋ በአራቱም አቅጣጫ የ14 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ ለማከናወን ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን የጋምቤላ ከተማ ከንቲባ ሳይመን ሙን (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ከንቲባ ሳይመን ሙን (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የተጀመረውን የኮሪደርና የውስጥ ለውስጥ የመንገድ መሰረተ ልማት በማፋጠን ከተማዋን ለነዋሪዎቿና ለቱሪስት መዳረሻነት ምቹ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው።
የጋምቤላ ከተማ ብዙ ዓመታትን ያስቆጠረችና የንግድ ቀጠና የነበረች ታሪካዊ ከተማ ብትሆንም የእድሜዋን ያህል ያላደገችና የመንገድ መሰረተ ልማት ችግር ያለባት ከተማ መሆኗንም አስታውሰዋል።
ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የከተሞች ልማት ስትራቴጂ ፖሊሲን ታሳቢ በማድረግ መንገድና ሌሎች የመሰረተ ልማት አውታሮችን ለማሟላት ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይ የከተሞች የኮሪደር ልማትን በማጠናከር ከተማዋን ውብ፣ጽዱና ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በከተማዋ በመጀመሪያው ዙር በተለያዩ አቅጣጫዎች የ14 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ በአራት ምዕራፍ ተከፋፍሎ ለመገንባት ግብ ተይዞ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።
በከተማው እየተከናወነ ባለው የኮሪደር ልማት የሥራ ዕድል ካገኙ ዜጎች መካከል ወጣት ሳዳም አብዱ በሰጠው አስተያየት፥ የኮሪደር ልማት ለከተማው እድገት ከሚኖረው ፋይዳ ባለፈ የሥራ እድል ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን ተናግሯል።
ኮሪደር ልማት የአካባቢን ገጽታ ለመቀየርና ስራ አጥ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መርሃ ግብር መሆኑን የገለጸው ደግሞ ሌላው በከተማው ኮሪደር ልማት እየተሳተፈ ያለው ወጣት ኑርሴን አብዱልቃደር ነው።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026