የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የጋምቤላ ከተማን የኮሪደር ልማት በማፋጠን ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ እየተሰራ ነው

Jun 4, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ግንቦት 27/2017 (ኢዜአ)፦የኮሪደር ልማቱን በማፋጠን ከተማዋን ለነዋሪዎቿና ለቱሪዝም ምቹ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የጋምቤላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ገለጹ።

በከተማዋ በአራቱም አቅጣጫ የ14 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ ለማከናወን ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን የጋምቤላ ከተማ ከንቲባ ሳይመን ሙን (ዶ/ር) ገልጸዋል።

ከንቲባ ሳይመን ሙን (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የተጀመረውን የኮሪደርና የውስጥ ለውስጥ የመንገድ መሰረተ ልማት በማፋጠን ከተማዋን ለነዋሪዎቿና ለቱሪስት መዳረሻነት ምቹ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው።

የጋምቤላ ከተማ ብዙ ዓመታትን ያስቆጠረችና የንግድ ቀጠና የነበረች ታሪካዊ ከተማ ብትሆንም የእድሜዋን ያህል ያላደገችና የመንገድ መሰረተ ልማት ችግር ያለባት ከተማ መሆኗንም አስታውሰዋል።

ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የከተሞች ልማት ስትራቴጂ ፖሊሲን ታሳቢ በማድረግ መንገድና ሌሎች የመሰረተ ልማት አውታሮችን ለማሟላት ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይ የከተሞች የኮሪደር ልማትን በማጠናከር ከተማዋን ውብ፣ጽዱና ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በከተማዋ በመጀመሪያው ዙር በተለያዩ አቅጣጫዎች የ14 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ በአራት ምዕራፍ ተከፋፍሎ ለመገንባት ግብ ተይዞ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።

በከተማው እየተከናወነ ባለው የኮሪደር ልማት የሥራ ዕድል ካገኙ ዜጎች መካከል ወጣት ሳዳም አብዱ በሰጠው አስተያየት፥ የኮሪደር ልማት ለከተማው እድገት ከሚኖረው ፋይዳ ባለፈ የሥራ እድል ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን ተናግሯል።

ኮሪደር ልማት የአካባቢን ገጽታ ለመቀየርና ስራ አጥ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መርሃ ግብር መሆኑን የገለጸው ደግሞ ሌላው በከተማው ኮሪደር ልማት እየተሳተፈ ያለው ወጣት ኑርሴን አብዱልቃደር ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026