
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2017(ኢዜአ)፦ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የተያዘውን ራዕይ እውን ለማድረግ በተከናወኑ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ገለጹ።
የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣን በጥራት መንደር ውስጥ የተረከበውን ህንጻ ምርቃት መርሃ ግብር አካሂዷል።

በመድረኩ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር)፣ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሰለሞን ጌታቸው እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ በለጠ ሞላ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የተያዘውን ራዕይ እውን ለማድረግ በተከናወኑ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ ነው።

የጥራት መንደሩ ለኢኮኖሚ ዕድገት ጉልህ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን አንስተው፤ መንደሩ ለኢኮኖሚ ዕድገት ወሳኝ የሆኑ ተቋማት በቅንጅት የሚሰሩበት መሆኑን ጠቁመዋል።
ይህም ኢትዮጵያን በአፍሪካ በጉልህ የሚያስቀምጣት መሰረተ ልማት መሆኑን ተናግረዋል።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣን በጥራት መንደር እንዲገቡ ከተፈለጉ ተቋማት መካከል አንዱ መሆኑን ገልጸዋል።
የጥራት መንደር የኢትዮጵያን የልማት መሻት የዋጀ የነገ ፍላጎታችንም ማሳያ እንዲሁም ለትውልድ የሚተርፍ ጸጋ መሆኑን ገልጸዋል።
የባለስልጣኑ ሰራተኞች በግቢው ያሉ መሰረተ ልማቶች እንዲጠበቁ የራሳቸውን ሚና እንዲወጡም አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሰለሞን ጌታቸው የተረከቡት ህንጻ ባለስልጣኑ የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ መወጣት የሚያስችለው መሆኑን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026