የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የኮሪደር ልማት ስራው የቡታጅራ ከተማን ለስራና ለመዝናኛ ምቹ አድርጓታል

Jun 5, 2025

IDOPRESS

ቡታጅራ፣ ግንቦት 27/2017 (ኢዜአ) ፡-በቡታጅራ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ለስራና ለመዝናኛ ምቹ እንዳደረጋት የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ።

በቡታጅራ ከተማ 25 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ስራ በህዝቡና በአስተዳደሩ የጋራ ትብብር እየተከናወነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታውቋል።


አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የቡታጅራ ከተማ ነዋሪዎች እንዳሉት እየተሰራ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ከተማዋን ለኑሮ ምቹና ሳቢ እያደረጋት ነው።

ከከተማው ነዋሪዎች መካከል አቶ ሽመልስ ለማ እንዳሉት ነዋሪው ለልማትና ለሰላም የማይደራደርና ከመንግስት ጋር ተባብሮ በመስራት የሚታወቅ ነው።

ለዚህም ህዝቡ የሚጠበቅበትን ግዴታ እየተወጣ ነው ያሉት ነዋሪው የኮሪደር ልማቱ ምቹ የመዝናኛ ስፍራ እንድናገኝ አድርጎናል ብለዋል።


ሌላው አስተያየት ሰጪ አቶ ይሳቅ ፈሪድ በበኩላቸው በአሁኑ ወቅት በከተማው እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የብስክሌት፣ የተሽከርካሪና የእግረኛ መንገድ በተለያየ ሁኔታ የያዘ በመሆኑ ለእግረኛና ለተሽከርካሪ ምቹ ሁኔታን የፈጠረ ነው ብለዋል።

ከተማዋ ከፍተኛ የንግድ እንቅስቃሴ የሚካሄድባት በመሆኑ ለንግድ ልውውጥ የሚመጡ እንግዶችም ከንግድ ስራቸው ባለፈ በከተማዋ ተጨማሪ ጊዜን እንዲያሳልፉ የኮሪደር ልማቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳበረከተም አመልክተዋል።

በኮሪደር ልማቱ የስራ ዕድል ከተፈጠረላቸው ነዋሪዎች መካከል ወጣት ግዛቸው አብረሃም በግንበኝነት ሙያ በተፈጠረለት የስራ ዕድል ገቢ እያገኘ መሆኑን ተናግሯል፡፡

በኮሪደር ልማቱ ላይ አሻራውን በማሳረፍ የመኖሪያ ከተማው ውብና ሳቢ ተደርጎ እየተገነባ በመሆኑደስተኛ እንዳደረገውም ጠቁሟል።


የቡታጀራ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዶ አህመድ በከተማው 25 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ሥራ ህብረተሰቡን በማሳተፍ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በእስካሁኑ ሂደት 8 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የስራው ክፍል መጠናቀቁን ተናግረዋል።

በህዝቡና በከተማ አስተዳደሩ ትብብር እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ሥራ ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት እንደተመደበ ጠቁመዋል።

የኮሪደር ልማት ሥራው በሚከናወንባቸው አካባቢዎች ህዝቡ ደስተኛ ሆኖ ንብረቱን በማንሳት የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ገልጸው ልማቱ በቡታጀራ ከተማ የሚካሄደውን ከፍተኛ የንግድ እንቅስቃሴና የቱሪስት ፍሰት እንዲጨምር ማድረጉን ገልፀዋል።

ስራውም የአረንጓዴ ልማት፣ የመዝናኛ ስፍራዎች፣ የእግረኛ መንገዶች፣ የብስክሌት መንገድና መናፈሻዎችን ባካተተ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ከንቲባው ጠቁመዋል።

በእነዚህ ስራዎች ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን ጠቅሰው፣ የመጀመሪያው ዙር የኮሪደር ልማት ሰኔ 30 ተጠናቆ ለምረቃ ይበቃል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025