
አዲስ አበባ፤ግንቦት 27/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ቤልጅየም የቢዝነስ ፎረም ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጮች እንድንመለከት አስችሎናል ሲሉ የቤልጂየምና ሉግዘምበርግ ንግድ ምክር ቤት ዋና ስራ አስፈፃሚ ቶማስ ዴቡል ገለጹ፡፡
የኢትዮ-ቤልጅየም የቢዝነስ ፎረም ግንቦት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች እና አምባሳደሮች በተገኙበት በአዲስ አበባ ከተማ መካሔዱ ይታወቃል።
በፎረሙ ኢትዮጵያውያንና ከቤልጂየም የመጡ በተለያዩ የኢንቨሰትመንት ዘርፎች የተሰማሩ ነጋዴዎች ምርቶቻቸውንና አገልግሎታቸውን አስተዋውቀዋል፡፡
በማጠቃለያው፥ የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት እና የቤልጄዬም ንግድ ምክር ቤት በተለያዩ መስኮች በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡

የቤልጄምና የሉግዘምበርግ ንግድ ምክር ቤት ዋና ስራ አስፈጻሚ ቶማስ ዴቡል በዚሁ ወቅት፤ ፎረሙ ኢትዮጵያ በፈጣን ኢኮኖሚያዊ እድገት ላይ መሆኗንና ያላትን ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጮች እንድንመለከት አስችሎናል ብለዋል፡፡
ከኢትዮጵያውያን ነጋዴዎች ጋርም ይበልጥ እንድንተዋወቅ እና የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ትልቅ እድል እንደፈጠረላቸውም አመላክተዋል፡፡
ስምምነቱ በሀገራቱ መካከል ያለውን የንግድና ኢንቨስትመንት እድሎች ለማሳደግ እና ለማስተዋወቅ የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
በግብርና፣በታዳሽ ሃይል፣በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በጤና፣ በሌሎች ዘርፎች ላይ ለመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው አመላክተዋል፡፡

የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ዘሐራ መሐመድ በበኩላቸው፥አዲስ ቻምበር በአገራቱ ነጋዴዎች መካከል እንደ ድልድይ ሆኖ የማገናኘት ሚናዎችን ይወጣል ብለዋል፡፡
ስምምነቱ ኢትዮጵያ ከቤልጅዬም እና ከሉግዘምበርግ ጋር ያላትን የቢዝነስ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በቀጣይ የቤልጅየም ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያለውን የኢንቨስትመንት እድል እንደሚጠቀሙ እና የንግድ ለንግድ ግንኙነት እንዲጠናከር ምክር ቤቱ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ተናግረዋል፡፡
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026