የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

አመራሩ በለውጥ እሳቤ ታግዞ ለውጥ ፈጣሪ ማህበረሰብ የመፍጠር ሃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት አለበት - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል

Jun 5, 2025

IDOPRESS

አርባ ምንጭ፤ ግንቦት 27/2017(ኢዜአ)፦ አመራሩ በለውጥ እሳቤ ታግዞ ለውጥ ፈጣሪ ማህበረሰብ የመፍጠር ሃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት እንዳለበት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል አስታወቁ።

በአርባ ምንጭ ከተማ ለሦስት ቀናት ሲሰጥ የቆየው የፐብሊክ ኢንተርፕሪነርሽፕና ኢኖቬሽን ስነ-ምህዳር ግንባታ የአመራሮች ስልጠና ተጠናቋል።


በማጠቃለያ መድረኩ የተገኙት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ባስተላለፉት መልዕክት አመራሩ በለውጥ እሳቤ ታግዞ ለውጥ ፈጣሪ ማህበረሰብ የመፍጠር ሃላፊነቱን በአግባቡ ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

የበለጸገ ክልልና ሀገር እንዲፈጠር በየደረጃው ያለው አመራር ጊዜውን የዋጀ የዕውቀትና ክህሎት ትጥቅ በመታጠቅ ለህብረተሰቡ ፈጠራ የታከለበት የሥራ ምህዳር መፍጠር ይኖርበታል ሲሉም አክለዋል።

በማያቋርጥ የለውጥ ሂደት ውስጥ ነን ያሉት ሚኒስትሯ፣ አመራሩ በየአካባቢው ያሉ ፀጋዎች ለህዝብ ጥቅም እንዲውሉ በማድረግ ታሪካዊ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበትም አስገንዝበዋል።

የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ከመንግስት ሀብት የሚፈልጉ ሳይሆን የራሳቸውን ሀብት የሚፈጥሩ መሆን እንዳለባቸው ጠቁመው፣ በየአካባቢው ያሉ ፀጋዎችን ጥቅም ላይ ለማዋል በሚሰራው ሥራ በቴክኖሎጂ ሽግግር የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው ገልጸዋል።

በለውጥ እሳቤ መሰረት የሥራ ዕድልን ከፈጠራ ጋር በማስተሳሰር ውጤታማ ሥራዎችን ለማከናወን ከአመራሩ ብዙ ይጠበቃል ሲሉም ተናግረዋል።


የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው የአመራር ስልጠና በሀገር ደረጃ የተጀመረውን የለውጥ እሳቤ በአግባቡ በመረዳት ለችግሮች ሀገር በቀል መፍትሄ መስጠት እንደሚያስችል ገልጸዋል።

ባለፉት ሰባት ዓመታት በሀገር ደረጃ የነበሩ ስብራቶችን ለመጠገን ሥራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸው፣ በዚህም ፈተናን ወደ ዕድል ዕዳን ወደ ምንዳ መቀየር ተችሏል ብለዋል።

በክልሉ ልማትን በማጠናከር ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ጸጋዎች እንዳሉ ጠቁመው፣ አመራሩ በስልጠና ባገኘው እውቀት ታግዞ ጸጋዎችን በማልማት ለሥራ አጥነት ችግር መፍትሄ መስጠት እንዳለበት አሳስበዋል።

ስልጠናውን ያልወሰዱ ቀሪ አመራሮችን በማሰልጠን የለውጡ እሳቤ ወጥነት ባለው መንገድ እንዲሳካ የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባም ጠቁመዋል።


የሥራ አጥነት ችግርን በቅጥር ብቻ ማስወገድ አይቻለም ያሉት የፌደራል ኢንተርፕሪነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን(ዶ/ር) ለዜጎች ምቹ የፈጠራ ምህዳር መፍጠር ያስፈልጋል ነው ያሉት።

ለወቅቱ ችግሮች ወቅቱን የሚመጥን መፍትሄ በመስጠት አመራሩ ስልጠናውን በተግባር ማሳየት እንዳለበትም ተናግረዋል።

በስልጠናው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እና በሥሩ የሚገኙ የ12 ዞኖች ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026