አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦ ባህርዳርን ወደ ምቹ የቱሪዝም፣ የአገልግሎትና የመኖሪያ ከተማነት ማሸጋገር የሚያስችሉ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባሀርዳር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል፡፡
ባህርዳርን ወደ ምቹ ከተማነት ለማሸጋገር የሚረዱ የመንገድ ግንባታ፣ የኮሪደር ልማትና የተቋማት ዕድሳት ስራዎች በከፍተኛ ርብርብ እየተከናወኑ መሆኑን መመልከታቸውንም ገልጸዋል።
በከተማዋ የሚገኙ የአማራ ክልል መንግሥት ተቋማት ምቹ የሥራና የአገልግሎት ከባቢ በመፍጠር ላይ መሆናቸው የሚደነቅ ተግባር ነው ብለዋል።
ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ለቱሪስቶች ተወዳጅና ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎች ይበል የሚያሰኙ ናቸው፡፡
የተጀመሩ መልካም ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ፣ በተጨማሪም ፕሮጀክቶችን በጥራት ለማጠናቀቅ እየተደረገ ያለውን ጥረት አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸዋል።
መንግስት የከተሞች ውበትና የተፈጥሮ ሀብቶች ተጠብቀው እንዲዘምኑና የቱሪስት መስህብነታቸው እንዲጨምር ለሚከናወኑ ተግባራት ድጋፍና ክትትሉን አጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025