
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦ ባህርዳርን ወደ ምቹ የቱሪዝም፣ የአገልግሎትና የመኖሪያ ከተማነት ማሸጋገር የሚያስችሉ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባሀርዳር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል፡፡
ባህርዳርን ወደ ምቹ ከተማነት ለማሸጋገር የሚረዱ የመንገድ ግንባታ፣ የኮሪደር ልማትና የተቋማት ዕድሳት ስራዎች በከፍተኛ ርብርብ እየተከናወኑ መሆኑን መመልከታቸውንም ገልጸዋል።

በከተማዋ የሚገኙ የአማራ ክልል መንግሥት ተቋማት ምቹ የሥራና የአገልግሎት ከባቢ በመፍጠር ላይ መሆናቸው የሚደነቅ ተግባር ነው ብለዋል።
ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ለቱሪስቶች ተወዳጅና ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎች ይበል የሚያሰኙ ናቸው፡፡

የተጀመሩ መልካም ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ፣ በተጨማሪም ፕሮጀክቶችን በጥራት ለማጠናቀቅ እየተደረገ ያለውን ጥረት አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸዋል።
መንግስት የከተሞች ውበትና የተፈጥሮ ሀብቶች ተጠብቀው እንዲዘምኑና የቱሪስት መስህብነታቸው እንዲጨምር ለሚከናወኑ ተግባራት ድጋፍና ክትትሉን አጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026