
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦ ባህርዳርን ወደ ምቹ የቱሪዝም፣ የአገልግሎትና የመኖሪያ ከተማነት ማሸጋገር የሚያስችሉ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባሀርዳር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል፡፡
ባህርዳርን ወደ ምቹ ከተማነት ለማሸጋገር የሚረዱ የመንገድ ግንባታ፣ የኮሪደር ልማትና የተቋማት ዕድሳት ስራዎች በከፍተኛ ርብርብ እየተከናወኑ መሆኑን መመልከታቸውንም ገልጸዋል።

በከተማዋ የሚገኙ የአማራ ክልል መንግሥት ተቋማት ምቹ የሥራና የአገልግሎት ከባቢ በመፍጠር ላይ መሆናቸው የሚደነቅ ተግባር ነው ብለዋል።
ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ለቱሪስቶች ተወዳጅና ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎች ይበል የሚያሰኙ ናቸው፡፡

የተጀመሩ መልካም ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ፣ በተጨማሪም ፕሮጀክቶችን በጥራት ለማጠናቀቅ እየተደረገ ያለውን ጥረት አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸዋል።
መንግስት የከተሞች ውበትና የተፈጥሮ ሀብቶች ተጠብቀው እንዲዘምኑና የቱሪስት መስህብነታቸው እንዲጨምር ለሚከናወኑ ተግባራት ድጋፍና ክትትሉን አጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026